ሚዲያ
በሶማሌ ክልል “ያለ ፈቃድ በጋዜጠኝነት ስራ ተሰማርተዋል” የተባሉ 15 መገናኛ ብዙሃን ታገዱ
በአማኑኤል ይልቃል
ከኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ባለስልጣን “ፈቃድ የላቸውም” የተባሉ 15 መገናኛ ብዙሃን እና ወኪሎቻቸው፤ በሶማሌ ክልል የሚያከናውኑትን የዘገባ ስራ እንዲያቆሙ ታዘዙ። የሶማሌ ክልል ጋዜጠኞች ማህበር፤ ከውሳኔው አስቀድሞ “ንግግር መደረግ ነበረበት” ሲል ተቃውሞውን አሰምቷል።
ውሳኔውን ከትላንት በስቲያ ቅዳሜ ጥር 20፤ 2015 በጻፈው ደብዳቤ ለመገናኛ ብዙሃኑ እና ወኪሎቻቸው ያስተላለፈው፤ የሶማሌ ክልል መንግስት ኮሚዩኒኬሽን...
መስከረም አበራ “በጥላቻ ንግግር” እና “በሐሰተኛ መረጃ ስርጭት” ክስ ተመሰረተባት
በሃሚድ አወል
የፌደራል ዐቃቤ ህግ የ“ኢትዮ ንቃት” የዩ-ቲዩብ መገናኛ ብዙኃን መስራች እና ባለቤት በሆነችው መስከረም አበራ እና አምሀ ደገፋ በተባሉ የስራ ባልደረባዋ ላይ “በጥላቻ ንግግር” እና “በሐሰተኛ መረጃ ስርጭት” ሁለት ክሶች መሰረተ። ክሱ የቀረበለት የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት፤ መስከረም ክሷን በውጭ ሆና እንድትከታተል የ50 ሺህ ብር ዋስትና ፈቅዷል።
ዐቃቤ ህግ ዛሬ...
የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት በመስከረም አበራ ላይ ክስ ለመመስረት ለዐቃቤ ህግ ሰባት ቀናት ፈቀደ
በሃሚድ አወል
ከሁለት ሳምንት ገደማ በፊት በፌደራል ፖሊስ ቁጥጥር ስር በዋለችው የ“ኢትዮ ንቃት” የዩቲዩብ መገናኛ ብዙሃን መስራች እና ባለቤት መስከረም አበራ ላይ ክስ የመመስረቻ ሰባት ቀናት በፍርድ ቤት ፈቀደ፡፡ ፍርድ ቤቱ የክስ መመስረቻ ቀናቱን የፈቀደው ዐቃቤ ህግ መስከረም በተጠረጠረችበት ጉዳይ የተሰባሰቡ “የቪዲዮ እና ሰነድ ማስረጃዎችን ለመተንተን ጊዜ እንደሚያስፈልገው በማመን” መሆኑን...
የጠቅላይ ሚኒስትር አብይን ግለ ታሪክ በመጽሐፍ ያሳተሙት ጋዜጠኛ፤ ዋልታ ሚዲያን እንዲመሩ ተሾሙ
በአማኑኤል ይልቃል
ከሶስት ዓመት በፊት ባሳተሙት የጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ግለ ታሪክ መጽሐፍ ይበልጥ የሚታወቁት አቶ መሐመድ ሐሰን፤ ዋልታ ሚዲያ እና ኮሚኒኬሽን ኮርፖሬትን እንዲመሩ ተሾሙ። አቶ መሐመድ ዋልታን በዋና ስራ አስፈጻሚነት እንዲመሩ የተሾሙት፤ የመገናኛ ብዙሃኑን ከ2011 ዓ.ም ጀምሮ ሲመሩ የቆዩት ዶ/ር ንጉሴ መሸሻን በመተካት ነው።
አዲሱን ሹመት በተመለከተ ጥያቄ የቀረበላቸው አቶ...
የኢዜአ የቦርድ አባላት ሹመት፤ በፓርላማ አባላት “የአሰራር እና የብዝሃነት” ጥያቄ ቀረበበት
በሃሚድ አወል
የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት (ኢዜአ) ቦርድ አባላት ሹመት ከተወካዮች ምክር ቤት አባላት የአሰራር (procedure) እና የብዝሃነት ጥያቄ ተነሳበት። የምክር ቤት አባላቱ ትላንት ሐሙስ ታህሳስ 13፤ 2015 በነበረው ስብሰባ “ሹመቱ ባለፈው ዓመት የተሰጠ ነው” የሚል አስተያየት አቅርበዋል።
ጥያቄዎችን እና አስተያየቶቹን ያሰሙት፤ የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ ፓርቲ (ኢዜማ) እና የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄን (አብን) ወክለው...
ሰለሞን ሹምዬ ከአምስት ሰዓታት እስር በኋላ ተለቀቀ
በሃሚድ አወል
ዛሬ ቅዳሜ ረፋድ በፌደራል ፖሊስ በቁጥጥር ስር የዋለው ሰለሞን ሹምዬ፤ ከአምስት ሰዓታት እስር በኋላ 10 ሰዓት ከ40 ገደማ መለቀቁን ቤተሰቦቹ ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናገሩ ። ሰለሞን ዛሬ አምስት ሰዓት ገደማ ላይ በፖሊስ ከተያዘ በኋላ፤ በአዲስ አበባ ገነት ሆቴል አቅራቢያ ወደሚገኘው “የፌደራል ፖሊስ የወንጀል ምርመራ ቢሮ መወሰዱን” እህቱ ትግስት ሹምዬ...
የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት፤ በመስከረም አበራ ላይ 14 የምርመራ ቀናት ፈቀደ
በሃሚድ አወል
ከትላንት በስቲያ ታህሳስ 4 በቁጥጥር ስር የዋለችው የ“ኢትዮ ንቃት” የዩቲዩብ መገናኛ ብዙኃን መስራች እና ባለቤት መስከረም አበራ ላይ 14 የምርመራ ቀናት ተፈቀደ። የምርመራ ቀናቱን ዛሬ ሐሙስ የፈቀደው የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ የጊዜ ቀጠሮ ችሎት ነው።
የፌደራል ፖሊስ ዛሬ የምርመራ ቀናቱን በጠየቀበት ወቅት መስከረም በተጠረጠረችበት “የሽብር ወንጀል ድርጊት”...
የካፋ ቴሌቪዥን፤ የሳተላይት መደበኛ ስርጭቱን ከሁለት ወራት በኋላ እንደሚጀመር አስታወቀ
በሃሚድ አወል
በኢትዮጵያ ተመዝግበው ፍቃድ ከተሰጣቸው የማህበረሰብ ቴሌቪዥን ጣቢያዎች ውስጥ አምስተኛ የሆነው የካፋ ቴሌቪዥን፤ ከሁለት ወራት በኋላ መደበኛ የሳተላይት ስርጭቱን ሊጀምር እንደሆነ አስታወቀ። የቴሌቪዥን ጣቢያው አማርኛ እና እንግሊዘኛን ጨምሮ በአምስት ቋንቋዎች ዜና እና ፕሮግራሞችን ለማስተላለፍ ማቀዱ ተገልጿል።
ከአንድ ወር ገደማ በፊት የ24 ሰዓት የሙከራ ስርጭቱን የጀመረው የካፋ ቴሌቪዥን፤ መደበኛ ዝግጅቶቹን ለመጀመር...
ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ በ30 ሺህ ብር ዋስትና ከእስር ተፈታ
በሃሚድ አወል
ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ከአምስት ወራት እስር በኋላ ዛሬ ረቡዕ ህዳር 7፤ 2015 ከቂሊንጦ ማረሚያ ቤት ተፈታ፡፡ተመስገን ከእስር የተፈታው፤ የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ በ30 ሺህ ብር ዋስትና እንዲፈታ መወሰኑን ተከትሎ ነው፡፡
ጋዜጠኛ ተመስገን የተፈታው ዛሬ ስምንት ሰዓት ተኩል ገደማ መሆኑን ወንድሙ ታሪኩ ደሳለኝ ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናግሯል፡፡ ከዛሬ ጠዋት ጀምሮ ቂሊንጦ ማረሚያ...
ጋዜጠኛ ጎበዜ ሲሳይ በመቶ ሺህ ብር ዋስትና ከእስር ተፈታ
በሃሚድ አወል
ጋዜጠኛ ጎበዜ ሲሳይ ከሁለት ወራት እስር በኋላ ዛሬ አርብ ህዳር 2፤ 2015 በመቶ ሺህ ብር ዋስትና ከእስር ተፈታ። ጋዜጠኛው ከእስር የተፈታው የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ይግባኝ ሰሚ ችሎት በስር ፍርድ ቤት የተፈቀደለትን ዋስትና ካጸና በኋላ ነው።
የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በትላንትናው ዕለት በነበረው የችሎት ውሎ፤ የስር ፍርድ ቤት ውሳኔን...
ተወካዮች ምክር ቤት፤ የኢቢሲ እና የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት አዳዲስ የቦርድ አባላትን ሹመት በአብላጫ ድምጽ...
በሃሚድ አወል
የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት፤ ለኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን (ኢቢሲ) እና ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት የቦርድ አባላትን ሹመት በአብላጫ ድምጽ አጸደቀ። የመንግስት ኮሚዩኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትሩ ዶ/ር ለገሠ ቱሉ የኢቢሲ ቦርድ ሰብሳቢ ሆነው ሲሾሙ፤ የጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ የማህበራዊ ዘርፍ አማካሪ የሆኑት ዲያቆን ዳንኤል ክብረት ደግሞ ለሶስት ተከታታይ ጊዜ በፕሬስ ድርጅት የቦርድ...
ጋዜጠኛ መዓዛ መሐመድ እና ደራሲ አሳዬ ደርቤ በዋስትና ከእስር ተፈቱ
በሃሚድ አወል
ከሁለት ሳምንት በፊት “ሀሰተኛ መረጃ በማሰራጨት ወንጀል” የተከሰሱት ጋዜጠኛ መዓዛ መሐመድ እና ደራሲ አሳዬ ደርቤ እያንዳንዳቸው 10 ሺህ ብር ዋስትና በማስያዝ፤ ዛሬ ሐሙስ ጥቅምት 3፤ 2015 ከእስር ተለቀቁ። ከሁለቱ ተከሳሾች ጋር በአንድ መዝገብ ክስ የተመሰረተበት ጋዜጠኛ ጎበዜ ሲሳይ ግን በፍርድ ቤት የተጣለበትን የጉዞ እግድ የተመለከተ ሰነድ ለፖሊስ ባለመቅረቡ...
በጋዜጠኛ ጎበዜ ሲሳይ፣ መዓዛ መሐመድ እና አሳዬ ደርቤ ላይ ክስ መመስረቱን ዐቃቤ ህግ አስታወቀ
በሃሚድ አወል
የፌደራል ዐቃቤ ህግ፤ በጋዜጠኛ ጎበዜ ሲሳይ፣ መዓዛ መሐመድ እና በደራሲ አሳዬ ደርቤ ላይ “የሃሰት ወሬን በመንዛት፤ በውጊያ ውስጥ የወገን ጦር አሰላለፍና ቦታን ለጠላት እና ለህዝብ በመሳወቅ” ወንጀል ክስ መመስረቱን የፍትህ ሚኒስቴር አስታወቀ። በሶስቱ ተጠርጣሪዎች ላይ ክስ መመስረቱ የተገለጸው፤ የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ዛሬ አርብ ሊመለከተው የነበረው የጊዜ ቀጠሮ...
ጋዜጠኛ መዓዛ መሐመድ እና ጎበዜ ሲሳይ “በሽብር ፈጠራ ወንጀል” መጠርጠራቸውን ፖሊስ አስታወቀ
በሃሚድ አወል
ከትላንት በስቲያ በቁጥጥር ስር የዋሉትን ጋዜጠኛ መዓዛ መሐመድ እና ጎበዜ ሲሳይን “በሽብር ፈጠራ ወንጀል” እንደጠረጠራቸው የፌደራል ፖሊስ ለፍርድ ቤት አስታወቀ። ጋዜጠኞቹ ከፌደራል መንግስቱ ጋር ሶስተኛ ዙር ውጊያ እያደረገ የሚገኘውን ህወሓትን በመደገፍም ተወንጅለዋል።
የፌደራል ፖሊስ ውንጀላውን ያቀረበውን ዛሬ አርብ ጷጉሜ 4፤ 2014 ለፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ የጊዜ ቀጠሮ...
ኢቢሲ በመጪው ዓመት ሶስት አዳዲስ የቴሌቪዥን ቻናሎችን ሊከፍት ነው
በሃሚድ አወል
የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን (ኢቢሲ) በመጪው 2015 ዓ.ም. ሶስት አዳዲስ የቴሌቪዥን ቻናሎችን ሊከፍት መሆኑን የኮርፖሬሽኑ ኃላፊዎች ተናገሩ። ትኩረቱን በህጻናት እና ታዳጊዎች ላይ ያደረገው አንደኛው የቴሌቪዥን ቻናል፤ በመስከረም ወር የመጀመሪያ ሳምንት የሙከራ ስርጭቱን ይጀምራል ተብሏል።
ብሔራዊ የሬድዮ እና የቴሌቪዥን ጣቢያዎችን በስሩ የሚያስተዳድረው ኢቢሲ፤ በአሁኑ ወቅት ሶስት የቴሌቪዥን ቻናሎች አሉት። የመጀመሪያው ቻናል...