ሚዲያ

ጋዜጠኛ በቃሉ አላምረው ለአራተኛ ጊዜ በፖሊስ ቁጥጥር ስር ዋለ 

በሃሚድ አወል “አልፋ ሚዲያ” የተሰኘው የበይነ መረብ መገናኛ ብዙሃን መስራች እና አዘጋጅ የሆነው ጋዜጠኛ በቃሉ አላምረው፤ ትላንት እሁድ ሐምሌ 30፤ 2015 የሁለተኛ ዲግሪ የምርቃት ስነ ስርዓት ተሳትፎ ወደ መኖሪያ ቤቱ ከተመለሰ በኋላ በጸጥታ ኃይሎች ቁጥጥር ስር መዋሉን ቤተሰቦቹ ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናገሩ። በጋዜጠኛ በቃሉ መኖሪያ ቤት ዛሬ ማለዳ ከ12፡30 ጀምሮ ለአንድ ሰዓት ያህል የቆየ ፍተሻ መካሄዱንም ቤተሰቦቹ ገልጸዋል።  ሶስት የፌደራል ፖሊስ የደንብ...

የወልቂጤ ኤፍ. ኤም ሬዲዮ ጣቢያ ሰራተኞች የሰኔ ወር ደመወዝ ስላልተከፈላቸው መቸገራቸውን ገለጹ  

በሃሚድ አወል በደቡብ ሬዲዮ እና ቴሌቪዥን ድርጅት ስር የሚገኘው የወልቂጤ ኤፍ. ኤም 89.2 ሬዲዮ ጣቢያ ሰራተኞች፤ የሰኔ ወር ደመወዝ እስካሁን ድረስ ስላልተከፈላቸው መቸገራቸውን ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር”...

የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ምክር ቤት፤ በመገናኛ ብዙሃን ላይ የሚፈጸሙ “ተደጋጋሚ” ዘረፋዎች “አሳስበውኛል” አለ 

በአማኑኤል ይልቃል በመገናኛ ብዙሃን ላይ የተፈጸሙ የዘረፋ ወንጀሎችን፤ መንግስት “በተቻለ ፍጥነት ተከታትሎ የምርመራውን ውጤት ለህዝብ ይፋ” እንዲያደርግ የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ምክር ቤት ጠየቀ። በመገናኛ ብዙሃን...

አራት የመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች እና ሌሎች 19 ተከሳሾች ያቀረቡት የዋስትና ጥያቄ በፍርድ ቤት ውድቅ...

በሃሚድ አወል በሽብር ወንጀል የተከሰሱ አራት የመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች እና ሌሎች 19 ተከሳሾች ያቀረቡት የዋስትና ጥያቄ፤ በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ውድቅ ተደረገ። የተከሳሾችን በቁጥጥር ስር መዋል በተመለከተ የጸጥታ እና ደህንነት የጋራ ግብረ ኃይል ያወጣውን መግለጫ በድረ ገጻቸው የጫኑ መገናኛ ብዙሃን ዘገባዎቻቸውን እንዲያወርዱም ፍርድ ቤቱ አዝዟል። ይህን ትዕዛዝ የሰጠው ዛሬ ረቡዕ ሐምሌ...

“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ቢሮ ውስጥ የተፈፀመውን ዘረፋ በተመለከተ ከሐቅ ሚዲያና ኮሚኒኬሽን የተሰጠ መግለጫ

በሐቅ ሚዲያና ኮሚኒኬሽን ሥር የሚተዳደረው “ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” የበይነመረብ ሚዲያ እሁድ፣ ሐምሌ 9፣ 2015 ለሰኞ አጥቢያ በቢሮው ውስጥ ያለ ካዝና ባልታወቁ አካላት ተሰብሮ፣ ንብረቱ ተዘርፏል። የሚዲያ ተቋሙ በሚሠራቸው ዘገባዎች ሳቢያ ተደጋጋሚ ጫናዎች እየደረሰበት ሲሆን፣ ይህ ዘረፋም የነዚህ ተደራራቢ ጫናዎች ተቀጥያ እንደሆነ ሐቅ ሚዲያና ኮሚኒኬሽን ያምናል።  ትላንት እሁድ የ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ባልደረቦች እስከ...

የ51 የሽብር ወንጀል ተከሳሾችን ጉዳይ የሚመለከቱ ዳኛ በሌላ መተካት፤ በችሎት ቅሬታ አስነሳ 

በሃሚድ አወል አምስት የመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎችን ጨምሮ የ51 የሽብር ወንጀል ተከሳሾችን ጉዳይ ከሚመለከቱት ዳኞች መካከል አንዱ መቀየራቸው በተከሳሾች እና ጠበቆቻቸው በኩል ቅሬታን አስነሳ። ጉዳዩን በተለመከተ በጽህፈት ቤት ቅሬታ የቀረበላቸው የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት፤ “ዳኞችን መቀየር የፍርድ ቤቱ አስተዳደር ስልጣን ነው” ሲሉ ለጠበቆች ምላሽ ሰጥተዋል ተብሏል። የፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ...

ዓለም አቀፉ የጋዜጠኞች መብት ተሟጋች፤ ጋዜጠኛ ጎበዜ ሲሳይ በአፋጣኝ እንዲፈታ ጥሪ አቀረበ

የኢትዮጵያ ባለስልጣናት ጋዜጠኛ ጎበዜ ሲሳይን በአፋጣኝ እንዲፈቱ ዓለም አቀፉ የጋዜጠኞች መብት ተሟጋች ሲፒጄ (CPJ) ጥሪ አቀረበ። መቀመጫውን በአሜሪካ ኒውዮርክ ያደረገው የጋዜጠኞች መብት ተሟጋች ትላንት አርብ ባወጣው መግለጫ “በአገር ውስጥና በውጪ ያሉ የፕሬስ አባላትን ማዋከብ እንዲያቆሙ” ለኢትዮጵያ መንግስት ባለስልጣናት ጥሪ አስተላልፏል። “የአማራ ድምጽ” የተባለው በዩቲዩብ የሚተላለፍ የግል መገናኛ ብዙኃን መስራች እና አርታኢ...

የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት፤ በጋዜጠኛ ዳዊት በጋሻው እና ቴዎድሮስ አስፋው ላይ ተጨማሪ የምርመራ ቀናት...

በሃሚድ አወል በጋዜጠኛ ዳዊት በጋሻው እና ቴዎድሮስ አስፋው ላይ ለሁለተኛ ጊዜ 14 ተጨማሪ የምርመራ ቀናት በፍርድ ቤት ተፈቀደ። የምርመራ ቀናቱን የፈቀደው ዛሬ አርብ ግንቦት 4፤ 2015 የዋለው፤ የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ የጊዜ ቀጠሮ ችሎት ነው። የጊዜ ቀጠሮ ችሎቱ የ“አራት ኪሎ ሚዲያ” የዩ ቲዩብ መገናኛ ብዙሃን መስራች ጋዜጠኛ ዳዊት በጋሻው...

ኢትዮጵያ በዓለም የፕሬስ ነጻነት ዝርዝር በ16 ደረጃዎች አሽቆለቆለች 

በተስፋለም ወልደየስ ድንበር የለሽ የጋዜጠኞች መብት ተሟጋች ድርጅት (RSF) በዓመቱ በሚያወጣው የዓለም የፕሬስ ነጻነት ዝርዝር፤ ኢትዮጵያ ዘንድሮ 130ኛ ደረጃ አገኘች። የ180 ሀገራት የፕሬስ ነጻነት በሚመዘንበት በዚህ ዝርዝር፤ ኢትዮጵያ አምና ከነበራት በ16 ደረጃዎች አሽቆልቁላለች።  መቀመጫውን በፓሪስ ፈረንሳይ ያደረገው የጋዜጠኞች መብት ተሟጋች ድርጅቱ፤ ይህን የሀገራት ደረጃ ላለፉት 20 ዓመታት ሲያወጣ ቆይቷል። በየሀገራቱ...

በኢትዮጵያ የመገናኛ ብዙሃን ነጻነት “በጉልህ ጥቃት ስር” እንደሚገኝ አንድ ዳሰሳ አመለከተ 

በተስፋለም ወልደየስ ባለፈው የፈረንጆቹ ዓመት ብቻ 29 ጋዜጠኞች በታሰሩባት ኢትዮጵያ፤ የፕሬስ ነጻነት “ጉልህ ጥቃት” እንዳጋጠመው ዓለም አቀፉ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅት አምነስቲ ኢንተርናሽናል እና የደቡባዊ አፍሪካ ሚዲያ ኢንስቲትዩት አስታወቁ። ባለስልጣናት የፕሬስ ነጻነትን ማፈን በሚፈልጉባቸው በምስራቅ እና ደቡባዊ አፍሪካ ሀገራት፤ በጋዜጠኞች ላይ የሚደርሰው ጥቃት እየጨመረ መምጣቱንም ተቋማቱ ገልጸዋል። ሁለቱ ተቋማት ይህን ያሉት...

የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት፤ በመስከረም አበራ ላይ 10 ተጨማሪ የምርመራ ቀናትን ፈቀደ

በሃሚድ አወል “ሁከት እና ብጥብጥ በማነሳሳት ወንጀል” ተጠርጥራ ከሁለት ሳምንት በፊት በፖሊስ ቁጥጥር ስር በዋለችው መስከረም አበራ ላይ አስር የምርመራ ቀናት በፍርድ ቤት ተፈቀደ። “ኢትዮ ንቃት” የተሰኘው የዩ-ቲዩብ መገናኛ ብዙኃን መስራች እና ባለቤት የሆነችው መስከረም፤ “ረዣዥም የጊዜ ቀጠሮ የሚጠየቅብኝ ወጥቼ የጋዜጠኝነት ስራዬን እንዳልሰራ ነው” ስትል ለፍርድ ቤት ተናግራለች።  የመስከረምን ጉዳይ እየተመለከተ...

ጋዜጠኞች ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ ተፈቅዶባቸው እንዲታሰሩ መደረጉ፤ “በምንም መለኪያ ተቀባይነት የሌለው ነው” ሲል የኢትዮጵያ...

በአማኑኤል ይልቃል ከስራቸው ጋር በተያያዘ በቁጥጥር ስር በዋሉ ጋዜጠኞች ላይ የቀረቡ ክሶችን፤ የፍትህ ስርዓቱ “በመገናኛ ብዙኃን አዋጅ ብቻ” በመመራት እንዲመለከታቸው የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ምክር ቤት ጠየቀ። በቁጥጥር ስር የዋሉ ጋዜጠኞች “እንደማንኛውም ተከሳሽ” ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ ተፈቅዶባቸው እንዲታሰሩ መደረጉንም፤ ምክር ቤቱ “በምንም መለኪያ ተቀባይነት የሌለው” ሲል ተችቷል።  የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ምክር ቤት ይህን...

ጋዜጠኛ ዳዊት በጋሻው እና ቴዎድሮስ አስፋው፤ “ሕገ መንግስታዊ ስርዓቱን በኃይል ለመናድ” በመንቀሳቀስ መጠርጠራቸውን ፖሊስ...

በሃሚድ አወል የ“አራት ኪሎ ሚዲያ” የዩ ቲዩብ መገናኛ ብዙሃን መስራች ጋዜጠኛ ዳዊት በጋሻው እና “ኢትዮ ሰላም” የተሰኘው የዩ ቲዩብ መገናኛ ብዙሃን መስራች ቴዎድሮስ አስፋው፤ “በህዝብ የተመረጠን መንግስት እና ሕገ መንግስታዊ ስርዓቱን በኃይል ለመናድ” በመንቀሳቀስ መጠርጠራቸውን ፖሊስ ለፍርድ ቤት አስታወቀ። ሁለቱ የመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች፤ 10 የምርመራ ቀናት በፍርድ ቤት ተፈቅዶባቸዋል።  ባለፈው ረቡዕ...

በሚዲያ ጥፋት የተጠረጠሩ ታሳሪዎች በሙሉ፤ “ያለምንም ቅድመ ሁኔታ” ከእስር እንዲለቀቁ ኢሰመኮ አሳሰበ 

በአማኑኤል ይልቃል በመገናኛ ብዙሃን አማካኝነት ተፈጽሟል በተባለ ወንጀል የተጠረጠሩ ታሳሪዎች “በሙሉ ያለምንም ቅድመ ሁኔታ” ከእስር እንዲለቀቁ የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) አሳሰበ። የመንግስት የጸጥታ አካላት በፖለቲካ ፓርቲዎች መሪዎችና አባላት፣ በሚዲያ አባላት እንዲሁም  በማህበረሰብ አንቂዎች ላይ ካተኮረ “እስር እና ማዋከብ” እንዲቆጠቡም ኮሚሽኑ ጠይቋል። ኢሰመኮ ይህንን ማሳሰቢያ የሰጠው፤ የመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች፣ የማህበረሰብ አንቂዎች...

መንግስት “ያለምንም የህግ አግባብ” ያሰራቸውን ጋዜጠኞች “በአስቸኳይ እንዲፈታ” የመገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎች ማህበር ጠየቀ 

በተስፋለም ወልደየስ መንግስት “ያለምንም የህግ አግባብ” ያሰራቸውን የመገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎችን “በአስቸኳይ እንዲፈታ” የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎች ማህበር ዛሬ አርብ ሚያዝያ 6፤ 2015 ባወጣው መግለጫ ጠየቀ። መንግስት በመገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎች ላይ የሚያደርሰውን ማሸማቀቅ እንዲያቆምም ማህበሩ ተመሳሳይ ጥያቄ አቅርቧል።   ማህበሩ በዛሬው መግለጫው፤ በኢትዮጵያ ከጊዜ ወደ ጊዜ የመገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎች የሚሰሩበት “አውድ እየጠበበ”...

የቀድሞው የ“አል አይን ኒውስ” ጋዜጠኛ፤ በባህር ዳር ከተማ በመከላከያ ሰራዊት አባላት ተይዞ መወሰዱን የዓይን...

በሃሚድ አወል እና በአማኑኤል ይልቃል “አራት ኪሎ ሚዲያ” የተሰኘው የዩቲዩብ መገናኛ ብዙሃን አዘጋጅ የሆነው ጋዜጠኛ ዳዊት በጋሻው፤ ዛሬ አመሻሽ ላይ በአማራ ክልል በባህር ዳር ከተማ በመከላከያ ሰራዊት አባላት ተይዞ መወሰዱን የዓይን እማኞች ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናገሩ። የመከላከያ ሰራዊት የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር ኮሎኔል ጌትነት አዳነ ስለ ጋዜጠኛው መያዝ መረጃ እንደሌላቸው ገልጸዋል። ጋዜጠኛው...

መስከረም አበራ “ለኢ-መደበኛ አደረጃጀቶች ወታደራዊ ስልጠና እና የተኩስ ልምምድ ስትሰጥ ነበር” ሲል ፖሊስ ወነጀለ...

በሃሚድ አወል ከትላንት በስቲያ እሁድ በፖሊስ ቁጥጥር ስር የዋለችው የመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዋ መስከረም አበራ፤ “ሁከት እና ብጥብጥ በማነሳሳት ወንጀል” ተጠርጥራ በፍርድ ቤት 13 የምርመራ ቀናት ተፈቀደባት። መስከረምን ፍርድ ቤት ያቀረባት የፌደራል ፖሊስ፤ “ተጠርጣሪዋ ለኢ-መደበኛ አደረጃጀቶች ወታደራዊ ስልጠና እና የተኩስ ልምምድ ስትሰጥ ነበር” ሲል ለፍርድ ቤቱ አስረድቷል።  ፖሊስ ዛሬ ማክሰኞ ሚያዚያ 3፤...

መስከረም አበራ ለሶስተኛ ጊዜ በፖሊስ ቁጥጥር ስር ዋለች 

በሃሚድ አወል “ኢትዮ ንቃት” የተሰኘው የዩ-ቲዩብ መገናኛ ብዙኃን መስራች እና ባለቤት የሆነችው መስከረም አበራ፤ ዛሬ እሁድ ሚያዝያ 1 አመሻሽ ላይ በፌደራል ፖሊስ በቁጥጥር ስር መዋሏን ባለቤቷ አቶ ፍጹም ገብረ ሚካኤል ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናገሩ። መስከረም በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ ለእስር ስትዳረግ የዛሬው ለሶስተኛ ጊዜ ነው።  በራሷም ሆነ በሌሎች መገናኛ ብዙኃን በምታቀርባቸው የፖለቲካ...