ሚዲያ
በኢትዮጵያ የመገናኛ ብዙሃን ነጻነት “በጉልህ ጥቃት ስር” እንደሚገኝ አንድ ዳሰሳ አመለከተ
በተስፋለም ወልደየስ
ባለፈው የፈረንጆቹ ዓመት ብቻ 29 ጋዜጠኞች በታሰሩባት ኢትዮጵያ፤ የፕሬስ ነጻነት “ጉልህ ጥቃት” እንዳጋጠመው ዓለም አቀፉ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅት አምነስቲ ኢንተርናሽናል እና የደቡባዊ አፍሪካ ሚዲያ ኢንስቲትዩት አስታወቁ። ባለስልጣናት የፕሬስ ነጻነትን ማፈን በሚፈልጉባቸው በምስራቅ እና ደቡባዊ አፍሪካ ሀገራት፤ በጋዜጠኞች ላይ የሚደርሰው ጥቃት እየጨመረ መምጣቱንም ተቋማቱ ገልጸዋል።
ሁለቱ ተቋማት ይህን ያሉት...
የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት፤ በመስከረም አበራ ላይ 10 ተጨማሪ የምርመራ ቀናትን ፈቀደ
በሃሚድ አወል
“ሁከት እና ብጥብጥ በማነሳሳት ወንጀል” ተጠርጥራ ከሁለት ሳምንት በፊት በፖሊስ ቁጥጥር ስር በዋለችው መስከረም አበራ ላይ አስር የምርመራ ቀናት በፍርድ ቤት ተፈቀደ። “ኢትዮ ንቃት” የተሰኘው የዩ-ቲዩብ መገናኛ ብዙኃን መስራች እና ባለቤት የሆነችው መስከረም፤ “ረዣዥም የጊዜ ቀጠሮ የሚጠየቅብኝ ወጥቼ የጋዜጠኝነት ስራዬን እንዳልሰራ ነው” ስትል ለፍርድ ቤት ተናግራለች።
የመስከረምን ጉዳይ እየተመለከተ...
ጋዜጠኞች ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ ተፈቅዶባቸው እንዲታሰሩ መደረጉ፤ “በምንም መለኪያ ተቀባይነት የሌለው ነው” ሲል የኢትዮጵያ...
በአማኑኤል ይልቃል
ከስራቸው ጋር በተያያዘ በቁጥጥር ስር በዋሉ ጋዜጠኞች ላይ የቀረቡ ክሶችን፤ የፍትህ ስርዓቱ “በመገናኛ ብዙኃን አዋጅ ብቻ” በመመራት እንዲመለከታቸው የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ምክር ቤት ጠየቀ። በቁጥጥር ስር የዋሉ ጋዜጠኞች “እንደማንኛውም ተከሳሽ” ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ ተፈቅዶባቸው እንዲታሰሩ መደረጉንም፤ ምክር ቤቱ “በምንም መለኪያ ተቀባይነት የሌለው” ሲል ተችቷል።
የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ምክር ቤት ይህን...
ጋዜጠኛ ዳዊት በጋሻው እና ቴዎድሮስ አስፋው፤ “ሕገ መንግስታዊ ስርዓቱን በኃይል ለመናድ” በመንቀሳቀስ መጠርጠራቸውን ፖሊስ...
በሃሚድ አወል
የ“አራት ኪሎ ሚዲያ” የዩ ቲዩብ መገናኛ ብዙሃን መስራች ጋዜጠኛ ዳዊት በጋሻው እና “ኢትዮ ሰላም” የተሰኘው የዩ ቲዩብ መገናኛ ብዙሃን መስራች ቴዎድሮስ አስፋው፤ “በህዝብ የተመረጠን መንግስት እና ሕገ መንግስታዊ ስርዓቱን በኃይል ለመናድ” በመንቀሳቀስ መጠርጠራቸውን ፖሊስ ለፍርድ ቤት አስታወቀ። ሁለቱ የመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች፤ 10 የምርመራ ቀናት በፍርድ ቤት ተፈቅዶባቸዋል።
ባለፈው ረቡዕ...
በሚዲያ ጥፋት የተጠረጠሩ ታሳሪዎች በሙሉ፤ “ያለምንም ቅድመ ሁኔታ” ከእስር እንዲለቀቁ ኢሰመኮ አሳሰበ
በአማኑኤል ይልቃል
በመገናኛ ብዙሃን አማካኝነት ተፈጽሟል በተባለ ወንጀል የተጠረጠሩ ታሳሪዎች “በሙሉ ያለምንም ቅድመ ሁኔታ” ከእስር እንዲለቀቁ የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) አሳሰበ። የመንግስት የጸጥታ አካላት በፖለቲካ ፓርቲዎች መሪዎችና አባላት፣ በሚዲያ አባላት እንዲሁም በማህበረሰብ አንቂዎች ላይ ካተኮረ “እስር እና ማዋከብ” እንዲቆጠቡም ኮሚሽኑ ጠይቋል።
ኢሰመኮ ይህንን ማሳሰቢያ የሰጠው፤ የመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች፣ የማህበረሰብ አንቂዎች...
መንግስት “ያለምንም የህግ አግባብ” ያሰራቸውን ጋዜጠኞች “በአስቸኳይ እንዲፈታ” የመገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎች ማህበር ጠየቀ
በተስፋለም ወልደየስ
መንግስት “ያለምንም የህግ አግባብ” ያሰራቸውን የመገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎችን “በአስቸኳይ እንዲፈታ” የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎች ማህበር ዛሬ አርብ ሚያዝያ 6፤ 2015 ባወጣው መግለጫ ጠየቀ። መንግስት በመገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎች ላይ የሚያደርሰውን ማሸማቀቅ እንዲያቆምም ማህበሩ ተመሳሳይ ጥያቄ አቅርቧል።
ማህበሩ በዛሬው መግለጫው፤ በኢትዮጵያ ከጊዜ ወደ ጊዜ የመገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎች የሚሰሩበት “አውድ እየጠበበ”...
የቀድሞው የ“አል አይን ኒውስ” ጋዜጠኛ፤ በባህር ዳር ከተማ በመከላከያ ሰራዊት አባላት ተይዞ መወሰዱን የዓይን...
በሃሚድ አወል እና በአማኑኤል ይልቃል
“አራት ኪሎ ሚዲያ” የተሰኘው የዩቲዩብ መገናኛ ብዙሃን አዘጋጅ የሆነው ጋዜጠኛ ዳዊት በጋሻው፤ ዛሬ አመሻሽ ላይ በአማራ ክልል በባህር ዳር ከተማ በመከላከያ ሰራዊት አባላት ተይዞ መወሰዱን የዓይን እማኞች ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናገሩ። የመከላከያ ሰራዊት የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር ኮሎኔል ጌትነት አዳነ ስለ ጋዜጠኛው መያዝ መረጃ እንደሌላቸው ገልጸዋል። ጋዜጠኛው...
መስከረም አበራ “ለኢ-መደበኛ አደረጃጀቶች ወታደራዊ ስልጠና እና የተኩስ ልምምድ ስትሰጥ ነበር” ሲል ፖሊስ ወነጀለ...
በሃሚድ አወል
ከትላንት በስቲያ እሁድ በፖሊስ ቁጥጥር ስር የዋለችው የመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዋ መስከረም አበራ፤ “ሁከት እና ብጥብጥ በማነሳሳት ወንጀል” ተጠርጥራ በፍርድ ቤት 13 የምርመራ ቀናት ተፈቀደባት። መስከረምን ፍርድ ቤት ያቀረባት የፌደራል ፖሊስ፤ “ተጠርጣሪዋ ለኢ-መደበኛ አደረጃጀቶች ወታደራዊ ስልጠና እና የተኩስ ልምምድ ስትሰጥ ነበር” ሲል ለፍርድ ቤቱ አስረድቷል።
ፖሊስ ዛሬ ማክሰኞ ሚያዚያ 3፤...
መስከረም አበራ ለሶስተኛ ጊዜ በፖሊስ ቁጥጥር ስር ዋለች
በሃሚድ አወል
“ኢትዮ ንቃት” የተሰኘው የዩ-ቲዩብ መገናኛ ብዙኃን መስራች እና ባለቤት የሆነችው መስከረም አበራ፤ ዛሬ እሁድ ሚያዝያ 1 አመሻሽ ላይ በፌደራል ፖሊስ በቁጥጥር ስር መዋሏን ባለቤቷ አቶ ፍጹም ገብረ ሚካኤል ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናገሩ። መስከረም በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ ለእስር ስትዳረግ የዛሬው ለሶስተኛ ጊዜ ነው።
በራሷም ሆነ በሌሎች መገናኛ ብዙኃን በምታቀርባቸው የፖለቲካ...
አዋጅን “በተጻረረ መንገድ” የተሾሙ የመገናኛ ብዙሃን ባለሥልጣን የቦርድ አባላት ከኃላፊነት እንዲነሱ ኢዜማ ጠየቀ
በአማኑኤል ይልቃል
ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ የመገናኛ ብዙሃን አዋጅን “በተጻረረ መንገድ” የሾሟቸውን የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ባለሥልጣን የቦርድ አባላት ከኃላፊነት እንዲያነሱ የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትህ (ኢዜማ) ጠየቀ። መንግስት የመገናኛ ብዙሃን ተቋማትን “ነጻ እና ገለልተኛ” ማድረግ ላይ ትኩረት አድርጎ እንዲሰራም ፓርቲው አሳስቧል።
ኢዜማ ይህንን ጥያቄ ያቀረበው፤ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ ከትላንት በስቲያ ማክሰኞ መጋቢት 19...
ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ከቀረበበት ክስ በፍርድ ቤት በነጻ ተሰናበተ
በሃሚድ አወል
የ“ፍትሕ” መጽሔት ማኔጂንግ ዳይሬክተር ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ፤ ከተከሰሰበት የሀሰተኛ መረጃ ማሰራጨት ወንጀል በነጻ ተሰናበተ። ጋዜጠኛው በነጻ የተሰናበተበትን ፍርድ የሰጠው፤ ዛሬ ረቡዕ የካቲት 29፤ 2015 የዋለው የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ አንደኛ የጸረ ሽብር እና ህገ መንግስታዊ ችሎት ነው።
የችሎቱን ፍርድ በንባብ ያሰሙት የግራ ዳኛ “ተከሳሹ የቀረበበትን ወንጀል በመከላከሉ...
ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ በቀረበበት ክስ ላይ ፍርድ ለመስጠት ቀጠሮ ተሰጠ
በሃሚድ አወል
የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ በቀረበበት ክስ ላይ ፍርድ ለመስጠት ለመጪው ሳምንት ረቡዕ የካቲት 29፤ 2015 ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጠ። የመከላከያ ሠራዊት “በተደጋጋሚ” ማስረጃ እንዲያቀርብ ትዕዛዝ ተሰጥቶት ባለማቅረቡ፤ ፍርድ ቤቱ ማስረጃውን ሳይመለከት ፍርድ ለመስጠት መወሰኑን አስታውቋል።
የፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ አንደኛ የጸረ ሽብር እና ህገ መንግስታዊ...
የደራሲ ሀዲስ አለማየሁ ወራሾች “ፍቅር እስከ መቃብር”ን በተመለከተ ለኢቢሲ የማስጠንቀቂያ ደብዳቤ አስገቡ
በአማኑኤል ይልቃል
የ“ፍቅር እስከ መቃብር” ደራሲ ሀዲስ አለማየሁ ወራሾች፤ የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን (ኢቢሲ) መጽሐፉን ወደ ተከታታይ የቴሌቪዥን ድራማ ቀይሮ “የማስተላለፍ መብት የለውም” ሲሉ ለተቋሙ የማስጠንቀቂያ ደብዳቤ አስገቡ። ይህ ደብዳቤ እንደደረሰው የገለጸው ኮርፖሬሽኑ፤ በጉዳዩ ላይ የተቋሙ አመራሮች ውይይት ካደረጉ በኋላ ተገቢውን ምላሽ እንደሚሰጥ አስታውቋል።
በ1958 ዓ.ም ለመጀመሪያ ጊዜ ለንባብ የበቃው “ፍቅር እስከ...
የሶማሌ ክልል ጋዜጠኞች ማህበር በክልሉ መንግስት ተሰጥቶት የነበረው ፈቃድ ተሰረዘ
በአማኑኤል ይልቃል
የሶማሌ ክልል ፍትህ ቢሮ “ተገቢ ያልሆነ ድርጊት ፈጽሟል” ያለውን የሶማሌ ክልል ጋዜጠኞች ማህበር ፈቃድ ሰረዘ። የሶማሌ ክልል ጋዜጠኞች ማህበር በበኩሉ እርምጃው “የመገናኛ ብዙሃንን ነጻነት ለማፈን የተወሰደ ነው” ሲል ውሳኔውን ነቅፏል።
በኢትዮጵያ ውስጥ ካሉ 24 የጋዜጠኛ ማህበራት ውስጥ አንዱ የሆነው የሶማሌ ክልል ጋዜጠኞች ማህበር የተመሰረተው ከሶስት ዓመት ገደማ በፊት በህዳር...
በሶማሌ ክልል “ያለ ፈቃድ በጋዜጠኝነት ስራ ተሰማርተዋል” የተባሉ 15 መገናኛ ብዙሃን ታገዱ
በአማኑኤል ይልቃል
ከኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ባለስልጣን “ፈቃድ የላቸውም” የተባሉ 15 መገናኛ ብዙሃን እና ወኪሎቻቸው፤ በሶማሌ ክልል የሚያከናውኑትን የዘገባ ስራ እንዲያቆሙ ታዘዙ። የሶማሌ ክልል ጋዜጠኞች ማህበር፤ ከውሳኔው አስቀድሞ “ንግግር መደረግ ነበረበት” ሲል ተቃውሞውን አሰምቷል።
ውሳኔውን ከትላንት በስቲያ ቅዳሜ ጥር 20፤ 2015 በጻፈው ደብዳቤ ለመገናኛ ብዙሃኑ እና ወኪሎቻቸው ያስተላለፈው፤ የሶማሌ ክልል መንግስት ኮሚዩኒኬሽን...