ሚዲያ

በኢትዮጵያ በጋዜጠኞች ላይ ስለሚፈጸመው ተደጋጋሚ እስር ሲፒጄ ምን አለ?

በኢትዮጵያ ከመጋቢት ወር አጋማሽ እስከ ሚያዝያ ወር አጋማሽ ባለው አንድ ወር ጊዜ ውስጥ ብቻ 14 ጋዜጠኞች እና የመገናኛ ብዙሃን ተቋማት ሰራተኞች ለእስር ተዳርገው እንደነበር ዓለም አቀፉ የጋዜጠኞች መብት ተሟጋች ድርጅት (ሲፒጄ) አስታወቀ። ከታሰሩት ጋዜጠኞች እና ሰራተኞች ውስጥ ሁለቱ አሁንም በእስር ላይ እንደሚገኙ ሲፒጄ ገልጿል። ሲፔጄ ይህን የገለጸው፤ በየሀገራቱ ያሉ ጋዜጠኞችን የተመለከቱ ሰሞነኛ ጉዳዮችን አጠናቅሮ ይፋ በሚያደርግበት ዘገባ ላይ ነው። ድርጅቱ...

የኢቢኤስ ቴሌቪዥን እና ሶስት የጣቢያው ሰራተኞች በጥላቻ ንግግር እና ሀሰተኛ መረጃ በማሰራጨት ተከሰሱ 

በተስፋለም ወልደየስ የኢቢኤስ ቴሌቪዥን፣ እህት ኩባንያው እና ሶስት የጣቢያው ሰራተኞች የጥላቻ ንግግር እና ሀሰተኛ መረጃ በማሰራጨት ወንጀል ክስ ቀረበባቸው። በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት በቀረበው በዚህ...

በኢትዮጵያ ሀሳብን የመግለጽ ነጻነት አሁንም “በከፍተኛ ጫና” ውስጥ እንደሆነ 14 ሀገራት በጋራ ባወጡት መግለጫ አስታወቁ 

ተቀማጭነታቸውን በአዲስ አበባ ያደረጉ የ14 ሀገራት ኤምባሲዎች፤ በኢትዮጵያ ሀሳብን በነጻነት መግለጽ ላይ ያለው “ከፍተኛ ጫና” መቀጠሉ እንደሚያሳስባቸው ገለጹ። በኢትዮጵያ የአውሮፓ ህብረት ተልዕኮ በበኩሉ የፕሬስ...

ፖሊስ በአራት የኢቢኤስ ቴሌቪዥን ሰራተኞች ላይ የጠየቀው የ14 ቀናት የምርመራ ጊዜ በፍርድ ቤት ተፈቀደለት

⚫ በተጨማሪ አራት የጣቢያው ሰራተኞች ላይ የቀረበው የጊዜ ቀጠሮ ጥያቄ ለነገ ተቀጥሯል በቤርሳቤህ ገብረ የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት፤ ፖሊስ “በሽብር ወንጀል ጉዳይ ጠርጥሬያቸዋለሁ” ባላቸው አራት የኢቢኤስ ቴሌቪዥን ጣቢያ ሰራተኞች ላይ የ14 ቀናት የምርመራ የጊዜ ቀጠሮ ፈቀደ። ባለፈው አርብ ፍርድ ቤት ከቀረቡ የጣቢያው ሰራተኞች መካከል፤ የካሜራ ባለሙያ የሆነው አቶ ቶማስ ደመቀ...

አምስት የኢቢኤስ ቴሌቪዥን ጣቢያ ሰራተኞች “በሽብር ወንጀል” ተጠርጥረው ፍርድ ቤት ቀረቡ

በቤርሳቤህ ገብረ የፌደራል ፖሊስ “በሽብር ወንጀል ጉዳይ” ጠርጥሬያቸዋለሁ ያላቸውን አምስት የኢቢኤስ ቴሌቪዥን ጣቢያ ሰራተኞችን በዛሬው ዕለት ፍርድ ቤት አቀረበ። ጉዳዩ የቀረበለት የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት፤ ፖሊስ በጠየቀው የ14 ቀናት የጊዜ ቀጠሮ ላይ ብይን ለመስጠት ለመጪው ሰኞ ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል። የፌደራል ፖሊስ የጊዜ ቀጠሮውን የጠየቀው፤ በስምንት ተጠርጣሪዎች ላይ እያካሄደ ያለውን የምርመራ ስራ...

የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለስልጣን አዲስ ዋና ዳይሬክተር ሊሾምለት ነው  

በተስፋለም ወልደየስ የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ካሉት ሰባት ምክትል ፕሬዝዳንቶች መካከል አንዱ የሆኑት ዶ/ር ሳምሶን መኮንን፤ የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለስልጣንን በዋና ዳይሬክተርነት እንዲመሩ በዕጩነት ቀረቡ። የአዲሱ ዋና ዳይሬክተር ሹመት ነገ ማክሰኞ ጥር 6፤ 2017 በሚካሄደው የፓርላማ መደበኛ ስብሰባ ላይ ይጸድቃል ተብሎ ይጠበቃል። የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የዋና ዳይሬክተሩን ሹመት እንዲያጸድቅ፤ ጥያቄውን ያቀረቡት...

ጋዜጠኛ በቃሉ አላምረው እና በላይ ማናዬ ከሀገር ተሰደዱ

በሙሉጌታ በላይ ከሶስት ወራት በፊት ከእስር የተፈቱት ጋዜጠኛ በቃሉ አላምረው እና በላይ ማናዬ፤ ሀገራቸውን ለቅቀው ለመሰደድ መገደዳቸውን ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር" ተናገሩ። ሁለቱ ጋዜጠኞቹ የተሰደዱት፤ በመንግስት የጸጥታ አባላት በተሰጣቸው “ለህይወታቸው የሚያሰጋ” “ማስጠንቀቂያ” እና ከእስር ከተፈቱ በኋላ በሚደረግባቸው “ክትትል” ምክንያት እንደሆነ ገልጸዋል። ጋዜጠኛ በላይ እና በቃሉ 11 ቀናት የፈጀ “አስቸጋሪ ጉዞ” በማድረግ ከሀገር...

ጋዜጠኛ በቃሉ አላምረው፣ በላይ ማናዬ እና ቴዎድሮስ ዘርፉ ከእስር ተፈቱ

በሙሉጌታ በላይ ለፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት “አካልን ነጻ የማውጣት” አቤቱታ ያቀረቡት ሶስት ጋዜጠኞች ከእስር ተፈቱ። ዛሬ እና ከትላንት በስቲያ ቅዳሜ ከእስር የተለቀቁት ጋዜጠኞች በቃሉ አላምረው፣ በላይ ማናዬ፣ ቴዎድሮስ ዘርፉ ናቸው።    ሶስቱ ጋዜጠኞች የፌደራል ፖሊስ “ሕገ መንግስታዊ መብታቸውን በመጣስ በእስር እንዲቆዩ” ማድረጉን በመጥቀስ ለፍርድ ቤት አቤቱታ ያቀረቡት ባለፈው ሳምንት ነበር።...

“ከአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ጋር በተያያዘ” በእስር ላይ የሚገኙ ሶስት ጋዜጠኞች “አካልን ነጻ የማውጣት” አቤቱታ...

በሙሉጌታ በላይ የተፈጻሚነት የጊዜ ወሰኑ ባለፈው ሳምንት ካበቃው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ጋር በተያያዘ በእስር ላይ የሚገኙ ሶስት ጋዜጠኞች፤ “አካልን ነጻ የማውጣት” (habeas corpus) አቤቱታ ለፍርድ ቤት አቀረቡ። አቤቱታውን በጠበቆቻቸው በኩል ለፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ያቀረቡት ጋዜጠኞች በቃሉ አላምረው፣ በላይ ማናዬ እና ቴዎድሮስ ዘርፉ ናቸው። ጋዜጠኞቹ አቤቱታውን ያቀረቡት፤ የፌደራል ፖሊስ “ሕገ...

ሀገር በቀሉ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅት፤ በኪነ ጥበብ ባለሙያዎች እና በጋዜጠኞች ላይ የሚፈጸመው “የዘፈቀደ...

በሙሉጌታ በላይ በጋዜጠኞች፣ በኪነ ጥበብ ባለሙያዎች፣ በማህበራዊ ሚዲያ ተጽእኖ ፈጣሪዎች እንዲሁም በፖለቲከኞች ላይ እየተፈጸመ ያለው “የዘፈቀደ እስር” እንዳሳሰበው “ስብስብ ለሰብአዊ መብቶች በኢትዮጵያ” የተሰኘው የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅት ገለጸ። እርምጃው “በአሳሳቢ ሁኔታ እየጠበበ የመጣውን የመገናኛ ብዙሃን ነጻነት እና ሀሳብን በነጻነት የመግለጽ መብት የማፈን አዝማሚያን የሚያመለክት ነው” ብሏል ድርጅቱ። ሀገር በቀሉ የሰብአዊ መብት...

በኢትዮጵያ ለአንድ ሳምንት የታሰረው ፈረንሳዊው ጋዜጠኛ አንቷን ጋሊንዶ ተለቀቀ

ላለፈው አንድ ሳምንት በአዲስ አበባ ከተማ በእስር ላይ የቆየው ፈረንሳዊው ጋዜጠኛ አንቷን ጋሊንዶ፤ ዛሬ ሐሙስ ከቀኑ 10 ሰዓት ገደማ ከእስር መለቀቁን ምንጮች ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ገለጹ። “አፍሪካ ኢንተለጀንስ” ለተሰኘው የዜና ድረ ገጽ ዘጋቢ የሆነው አንቷን፤ ዛሬ እኩለ ለሊት ገደማ ኢትዮጵያን ለቅቆ ወደ ሀገሩ መመለሱን ምንጮቹ ተናግረዋል። ጋዜጠኛው ከሁለት ሳምንት በፊት ወደ...

በጋዜጠኞች እስር፤ ኢትዮጵያ ከአፍሪካ ሃገራት ሶስተኛ ደረጃ ላይ መቀመጧን ሲፒጄ ገለጸ

ኢትዮጵያ ጋዜጠኞችን በማሰር ከአፍሪካ ሃገራት ሶስተኛ ደረጃ መያዟን ዓለም አቀፉ የጋዜጠኞች መብት ተሟጋች (ሲፒጄ) ባለፈው ሳምንት መጨረሻ ባወጣው ዓመታዊ ሪፖርቱ አስታውቋል። በአፍሪካ በታሳሪ ጋዜጠኞች ብዛት ቀዳሚውን ቦታውን የያዘችው የኢትዮጵያ ጎረቤት ኤርትራ ስትሆን፤ ግብጽ ሁለተኛ ቦታን ይዛለች።  ሲፒጄ ዓመታዊ ሪፖርቱን ባጠናቀረበት ባለፈው ህዳር ወር መጨረሻ ገደማ፤ በመላው ዓለም የታሰሩ ጋዜጠኞች ብዛት...

ኢቢሲ “ኢትዮጵያን አይመስልም” የሚል ትችት በፓርላማ አባላት ቀረበበት

ዛሬ ማክሰኞ ታህሳስ 9፤ 2016 በተካሄደው የፓርላማ መደበኛ ስብሰባ፤ አቶ ጌትነት ታደሰ የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን (ኢቢሲ) ዋና ስራ አስፈጻሚ ሆነው በሙሉ ድምጽ ተሹመዋል። አቶ ጌትነት አዲሱን ሹመት ከማግኘታቸው በፊት በነበሩት አምስት ዓመታት የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅትን በዋና ስራ አስፈጻሚነት ሲመሩ ቆይተዋል። በኢቢሲ አዲስ ዋና ስራ አስፈጻሚ ሹመት ላይ አስተያየታቸውን የሰጡ ሁለት...

ጋዜጠኛ በቃሉ አላምረው ለአራተኛ ጊዜ በፖሊስ ቁጥጥር ስር ዋለ 

በሃሚድ አወል “አልፋ ሚዲያ” የተሰኘው የበይነ መረብ መገናኛ ብዙሃን መስራች እና አዘጋጅ የሆነው ጋዜጠኛ በቃሉ አላምረው፤ ትላንት እሁድ ሐምሌ 30፤ 2015 የሁለተኛ ዲግሪ የምርቃት ስነ ስርዓት ተሳትፎ ወደ መኖሪያ ቤቱ ከተመለሰ በኋላ በጸጥታ ኃይሎች ቁጥጥር ስር መዋሉን ቤተሰቦቹ ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናገሩ። በጋዜጠኛ በቃሉ መኖሪያ ቤት ዛሬ ማለዳ ከ12፡30 ጀምሮ ለአንድ...

የወልቂጤ ኤፍ. ኤም ሬዲዮ ጣቢያ ሰራተኞች የሰኔ ወር ደመወዝ ስላልተከፈላቸው መቸገራቸውን ገለጹ  

በሃሚድ አወል በደቡብ ሬዲዮ እና ቴሌቪዥን ድርጅት ስር የሚገኘው የወልቂጤ ኤፍ. ኤም 89.2 ሬዲዮ ጣቢያ ሰራተኞች፤ የሰኔ ወር ደመወዝ እስካሁን ድረስ ስላልተከፈላቸው መቸገራቸውን ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናገሩ። በጉራጌ ዞን የሚገኘው የወልቂጤ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ሰራተኞች የሰኔ ወር ደመወዝ ክፍያ እንዳልተፈጸመላቸው ያረጋገጡት የደቡብ ሬዲዮ እና ቴሌቪዥን ድርጅት ስራ አስፈጻሚ ተወካይ፤ የተፈጠረው መስተጓጎል...

የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ምክር ቤት፤ በመገናኛ ብዙሃን ላይ የሚፈጸሙ “ተደጋጋሚ” ዘረፋዎች “አሳስበውኛል” አለ 

በአማኑኤል ይልቃል በመገናኛ ብዙሃን ላይ የተፈጸሙ የዘረፋ ወንጀሎችን፤ መንግስት “በተቻለ ፍጥነት ተከታትሎ የምርመራውን ውጤት ለህዝብ ይፋ” እንዲያደርግ የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ምክር ቤት ጠየቀ። በመገናኛ ብዙሃን ተቋማት ቢሮ እና መሳሪያዎች ላይ “ባልታወቁ ሰዎች በተቀናጀ እና የተናበበ በሚመስል መልኩ” የሚፈጸም ተደጋጋሚ ዘረፋ ጉዳዩን አሳሳቢ እንዳደረገው ምክር ቤቱ ገልጿል፡፡ የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ምክር ቤት...

አራት የመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች እና ሌሎች 19 ተከሳሾች ያቀረቡት የዋስትና ጥያቄ በፍርድ ቤት ውድቅ...

በሃሚድ አወል በሽብር ወንጀል የተከሰሱ አራት የመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች እና ሌሎች 19 ተከሳሾች ያቀረቡት የዋስትና ጥያቄ፤ በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ውድቅ ተደረገ። የተከሳሾችን በቁጥጥር ስር መዋል በተመለከተ የጸጥታ እና ደህንነት የጋራ ግብረ ኃይል ያወጣውን መግለጫ በድረ ገጻቸው የጫኑ መገናኛ ብዙሃን ዘገባዎቻቸውን እንዲያወርዱም ፍርድ ቤቱ አዝዟል። ይህን ትዕዛዝ የሰጠው ዛሬ ረቡዕ ሐምሌ...

“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ቢሮ ውስጥ የተፈፀመውን ዘረፋ በተመለከተ ከሐቅ ሚዲያና ኮሚኒኬሽን የተሰጠ መግለጫ

በሐቅ ሚዲያና ኮሚኒኬሽን ሥር የሚተዳደረው “ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” የበይነመረብ ሚዲያ እሁድ፣ ሐምሌ 9፣ 2015 ለሰኞ አጥቢያ በቢሮው ውስጥ ያለ ካዝና ባልታወቁ አካላት ተሰብሮ፣ ንብረቱ ተዘርፏል። የሚዲያ ተቋሙ በሚሠራቸው ዘገባዎች ሳቢያ ተደጋጋሚ ጫናዎች እየደረሰበት ሲሆን፣ ይህ ዘረፋም የነዚህ ተደራራቢ ጫናዎች ተቀጥያ እንደሆነ ሐቅ ሚዲያና ኮሚኒኬሽን ያምናል።  ትላንት እሁድ የ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ባልደረቦች እስከ...