ሰሞነኛ ጉዳዮች

የአፈር ማዳበሪያ አቅርቦት እና ስርጭት መዘግየት፤ ዘንድሮ በፓርላማ ማነጋገሩን ቀጥሏል

በቤርሳቤህ ገብረ የግብርና ሚኒስቴር ኃላፊዎች የሩብ፣ የመንፈቅ፣ የዘጠኝ ወር አሊያም የዓመት የስራ አፈጻጸም ሪፖርታቸውን ለማቅረብ ወደ ፓርላማ በሚመጡበት ጊዜ ሁልጊዜም ከአንድ ጉዳይ ጋር የተያያዙ በርከት ያሉ ጥያቄዎች ይቀርቡላቸዋል። ጉዳዩ አብዛኛውን የሀገሪቱን ህዝብ ብዛት የሚወክለውን አርሶ አደር በቀጥታ የሚመለከተው የአፈር ማዳበሪያ አቅርቦት እና ስርጭት ነው። የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ትላንት ሰኞ ጥር 19፤ 2017 ባካሄደው ልዩ ስብሰባ ላይ ይህ ጉዳይ ተነስቶ መወያያ...

የህዝብ ዕንባ ጠባቂ ተቋም አመራሮች ሹመት፤ የፓለቲካ ገለልተኝነትን “ጥያቄ ውስጥ ያስገባ ነው” የሚል ትችት ቀረበበት

በቤርሳቤህ ገብረ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ሹመታቸውን ያጸደቀላቸው የኢትዮጵያ የህዝብ ዕንባ ጠባቂ ተቋም አመራሮች የአመራረጥ ሂደት፤ “ከፓለቲካ ገለልተኝነት” ነጻ መሆን የሚለውን መስፈርት “ጥያቄ ውስጥ...

በጠለምት ወረዳ በመሬት መንሸራተት የተፈናቀሉ ነዋሪዎች፤ እርዳታ እና ዘላቂ የሰፈራ ቦታ ባለማግኘታቸው መቸገራቸውን ገለጹ

በደምሰው ሽፈራው የአማራ እና የትግራይ ክልሎች የይገባኛል ጥያቄ ከሚያነሱባቸው አካባቢዎች አንዱ በሆነው ጠለምት ወረዳ በመሬት መንሸራተት የተፈናቀሉ በሺህዎች የሚቆጠሩ ነዋሪዎች፤ ከአራት ወራት በኋላም “በጊዜያዊ መጠለያ...

በወላይታ ሶዶ ነዳጅ ማደያዎች የማይገኘው ቤንዚን፤ በከተማዋ ጎዳናዎች ላይ እንዴት እንደ ልብ ሊገኝ ቻለ?

በናሆም አየለ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የፖለቲካ እና የርዕሰ መስተዳድር መቀመጫ የሆነችው የወላይታ ሶዶ ከተማ፤ በሰባት በሮች እንግዶቿን ትቀበላለች። የህዝብ ትራንስፖርት እና የግል ተሽከርካሪዎችን የሚጠቀሙ ተጓዦች፤ በአረካ፣ ቦዲቲ፣ ኡምቦ እና ገሱባ ከተሞች አድርገው ወደ ወላይታ ሶዶ መግባት ይችላሉ። በጭዳ፣ ሆቢቻ፣ በዴሳ ከተሞች በኩል ያሉ መንገዶችን ለተጓዦች በአማራጭነት ያገለግላሉ።   ከአዲስ አበባ ከተማ 332...

ህወሓት አወዛጋቢውን 14ኛ ጠቅላላ ጉባኤ በመቐለ ከተማ ማካሄድ ጀመረ 

በተስፋለም ወልደየስ ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) በተለያዩ ወገኖች ተቃውሞ እና ትችት የተሰነዘረበትን የጠቅላላ ጉባኤ የመክፈቻ ስነ ስርዓት፤ ዛሬ ማክሰኞ ነሐሴ 7፤ 2016 በመቐለ ከተማ በሚገኘው የሰማዕታት ሐውልት አዳራሽ አካሄደ። ፓርቲው ጠቅላላ ጉባኤውን ያካሄደው ምክትል ሊቀመንበሩ አቶ ጌታቸውን ረዳን ጨምሮ 14 የማዕከላዊ ኮሚቴ አባላት ባልተገኙበት ነው።   ህወሓት ከስድስት ዓመት በኋላ...

ምርጫ ቦርድ ለህወሓት የህጋዊ ሰውነት ማረጋገጫ የምስክር ወረቀት ሰጠ 

በተስፋለም ወልደየስ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) የህጋዊ ሰውነት ማረጋገጫ የምስክር ወረቀት “በልዩ ሁኔታ” መስጠቱን አስታወቀ። ሆኖም ቦርዱ ህወሓት ያቀረበለትን “የቀድሞውን ህልውና ወደነበረበት የመመለስ” ጥያቄ አለመቀበሉን አስታውቋል። ብሔራዊው ምርጫ ቦርድ ይህን ያስታወቀው፤ የህወሓትን ህጋዊ እውቅና የማግኘት ጉዳይ በተመለከተ ዛሬ አርብ ነሐሴ 3፤ 2016 ባወጣው መግለጫ ነው።...

በድጋሚ እና ቀሪ ምርጫ፤ ተቃዋሚ ፓርቲዎች ሁለት የፓርላማ መቀመጫ አሸነፉ 

⚫ ከዘጠኝ ዓመት በኋላ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል አዲስ መንግስት ለመመስረት የሚያስችል ውጤት ይፋ ተደርጓል      በሙሉጌታ በላይ በሰኔ ወር አጋማሽ በአራት ክልሎች በተካሄደው “ቀሪ እና ድጋሚ ምርጫ”፤ ሁለት ተቃዋሚ ፓርቲዎች ሁለት የፓርላማ መቀመጫ አሸነፉ። በባለፈው ጠቅላላ ምርጫ ያልተደረገባቸውን አብዛኞቹን የክልል ምክር ቤት እና የፓርላማ መቀመጫዎች፤ ገዢው ብልጽግና ፓርቲ አሸንፏል። በአፋር፣...

በቤት ኪራይ ውድነት የተቸገሩ የመቐለ ዩኒቨርሲቲ መምህራን፤ በተማሪዎች ዶርም “በጊዜያዊነት” እየኖሩ ነው

በሙሉጌታ በላይ በትግራይ ክልል በሚገኘው መቐለ ዩኒቨርሲቲ የሚያስተምሩ የተወሰኑ መምህራን “ቤት ተከራይቶ መኖር እንደከበዳቸው” ለተቋሙ ማመልከታቸውን ተከትሎ፤ በተማሪዎች ማደሪያ ዶርም “በጊዜያዊነት” እንዲቆዩ ተፈቅዶላቸው እየኖሩ መሆኑን ገለጹ። የዩኒቨርስቲው መምህራን በክልሉ በነበረው ጦርነት ሳቢያ የ17 ወር ደመወዝ ያልተከፈላቸው መሆኑ፤ በአስር ሺህዎች የሚቆጠር ውዝፍ የቤት ኪራይ እንዲከማችባችው አድርጓል።   በ1992 ዓ.ም በወጣ ደንብ የተቋቋመው...

የጊዜ ገደቡ ስላበቃው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ፤ የኦፌኮ፣ የኢዜማ እና የእናት ፓርቲ አመራሮች ምን አሉ?...

በሙሉጌታ በላይ በአማራ ክልል ለአስር ወራት የቆየው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መፍትሔ እንዳላመጣ የኦሮሞ ፌደራላዊ ኮንግረስ (ኦፌኮ) እና እናት ፓርቲ ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ገለጹ። ሌላኛው ተቃዋሚ ፓርቲ የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትህ (ኢዜማ) ግን አዋጁ በክልሉ “የተወሰኑ መረጋጋት እንዲኖር አድርጓል” ሲል አስታውቋል። ተጠሪነቱ ለጠቅላይ ሚኒስትሩ የሆነው የሚኒስትሮች ምክር ቤት፤ በአማራ ክልል የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ...

“በአመጽ እና በህገ-ወጥ መንገድ ሲንቀሳቀስ የነበረ” የፖለቲካ ፓርቲ፤ ማመልከቻው በ15 ቀናት ውስጥ ተቀባይነት እንዲያገኝ...

በተስፋለም ወልደየስ “በአመጽ እና በህገ-ወጥ መንገድ ሲንቀሳቀስ የነበረ” የፖለቲካ ፓርቲ፤ “በልዩ ሁኔታ” ለመመዝገብ ማመልከቻ ባቀረበ “በ15 የስራ ቀናት ውስጥ ምዝገባው እንዲፈጸም” የሚያደርግ አዋጅ በነገው ዕለት ለፓርላማ ቀርቦ ሊጸድቅ ነው። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በዚህ መልኩ የቀረበለትን ማመልከቻ ውድቅ የማድረግ አማራጭ በአዋጁ ባይሰጠውም፤ በፓርቲው ላይ ለሁለት ዓመታት “ክትትል እና ቁጥጥር” የማድረግ...

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከፒያሳ ለሚነሱ የግል አልሚዎች “ካሳ እና ምትክ መሬት” እንደሚሰጥ አስታወቀ 

በተስፋለም ወልደየስ በአዲስ አበባ ፒያሳ አካባቢ ከተገነባው የአድዋ ድል መታሰቢያ ጎን በሚገኘው ቦታ ላይ የሚኖሩ ነዋሪዎች፤ ከስፍራው እንደሚነሱ የከተማይቱ ከንቲባ አዳነች አበቤ ማረጋገጫ ሰጡ። ለእነዚህ የልማት ተነሺዎች የከተማው አስተዳደር “የጋራ መኖሪያ ቤት” አሊያም “አዲስ የሚገነባ የቀበሌ ቤት” እንደ የምርጫቸው እንደሚያቀርብ፤ በአካባቢው በተዘጋጀው ፕላን መሰረት ግንባታ ለማከናወን የገንዘብ አቅም ለሌላቸው የግል...

በአዲስ አበባ ከተማ ፒያሳ አካባቢ የሚገኙ ነዋሪዎች በሶስት ወራት ጊዜ ውስጥ ከስፍራው ሊነሱ ነው  

በተስፋለም ወልደየስ በአዲስ አበባ ከተማ ፒያሳ አካባቢ በተለምዶ ዶሮ ማነቂያ ተብሎ በሚጠራው ቦታ የሚገኙ ነዋሪዎች፤ በሶስት ወራት ጊዜ ውስጥ ከስፍራው እንዲነሱ ቀነ ገደብ ተሰጣቸው። የከተማይቱ አስተዳደር ምትክ የመኖሪያ እና የንግድ ቦታ ሳያዘጋጅላቸው፤ ከስፍራው “በአጭር ጊዜ ውስጥ” ተነሱ ማለቱ በነዋሪዎቹ ዘንድ ከፍተኛ ቅሬታ ቀርቦበታል። ነዋሪዎቹ ይህን ቅሬታቸውን ያሰሙት፤ የአካባቢውን መልሶ ማልማት በተመለከተ...

ለ13 ዓመታት ያልተመለሰው የአየር ትራፊክ ተቆጣጣሪዎች ጥያቄ 

በተስፋለም ወልደየስ ጊዜው ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ወደ ስልጣን የመጡ ሰሞን ነው። አራት ኪሎ ከሚገኘው ጽህፈት ቤታቸው ከገቡ ገና አራተኛ ወራቸው። ወቅቱ መንግስትን እና ገዢውን ፓርቲ የሚመለከቱ፤ ከዚህ ቀደም በአደባባይ የማይደመጡ የተለያዩ የተቃውሞ እና ሞጋች ሀሳቦች እንደ ልብ የሚንሸራሸሩበት ነበር። በዚህ ጊዜ ነበር ባልተለመደ መልኩ በአንድ የመንግስት ቁልፍ ተቋም...

በመብት ተሟጋቾች የተተቸው የሊባኖስ እና የኢትዮጵያ ስምምነት ለፓርላማ ቀረበ 

በተስፋለም ወልደየስ የቤት ሰራተኞች መብት እንዲከበር የሚሟገቱ ግለሰቦች እና ተቋማት ትችት ሲያሰሙበት የቆየው፤ የኢትዮጵያ እና የሊባኖስ መንግስታት የስራ ስምሪት ስምምነት ለፓርላማ ቀረበ። በሁለቱ ሀገራት ስምምነት ላይ ለኢትዮጵያውያን የቤት ሰራተኞች የሚከፈለው ዝቅተኛ ደመወዝ አለመካተቱ በዛሬው የተወካዮች ምክር ቤት ስብሰባ ጥያቄ ተነስቶበታል። ኢትዮጵያ ከ300 ሺህ እስከ 400 ሺህ የሚገመቱ ዜጎቿ በቤት ሰራተኝነት ተቀጥረው...

ከተበተኑ የአማራ ክልል የልዩ ኃይል አባላት መካከል፤ “አብዛኛዎቹ” ታጣቂ ቡድኖችን መቀላቀላቸውን የሰላም ሚኒስትሩ ገለጹ...

በአማኑኤል ይልቃል በአማራ ክልል የልዩ ኃይል አባላትን ወደ ሌሎች የጸጥታ መዋቅሮች የማስገባት ስራ ከተጀመረ በኋላ 50 በመቶ የሚሆኑ የልዩ ኃይል አባላት “እንደተበተኑ” እና ከእነዚህ ውስጥ “አብዛኛዎቹ” ታጣቂ ቡድኖችን እንደተቀላቀሉ የሰላም ሚኒስትሩ አቶ ብናልፍ አንዷለም ተናገሩ። በአማራ ክልል ከሰሞኑ የተቀሰቀሰው ግጭት የተጀመረው፤ ታጣቂዎች በመከላከያ ሰራዊት ካምፕ ላይ “ዘግናኝ የሚባል ጥቃት መክፈታቸውን”...

የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች በተመረጠላቸው “የትኩረት መስክ” ብቻ እንዲያስተምሩ የሚያደርገው አዲስ አሰራር እንዴት ይተገበራል?  

በአማኑኤል ይልቃል በመላው ኢትዮጵያ የሚገኙ 47 የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች፤ ራስ ገዝ መሆንን ጨምሮ አዳዲስ አሰራሮችን ለመተግበር እየተዘጋጁ ይገኛሉ። “አጠቃላይ” የትምህርት ዘርፎችን ለተማሪዎች ሲሰጡ የቆዩት እነዚህን ዩኒቨርስቲዎች፤ ከሚቀጥለው ዓመት ጀምሮ በተለየላቸው “የተልዕኮ እና የትኩረት መስክ” ብቻ የሚያስተምሩ ተቋማት ለማድረግ እንቅስቃሴ መጀመሩን የትምህርት ሚኒስቴር አስታውቋል።  በሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ዕቅድ መሰረት፤ ከመንግስት ዩኒቨርስቲዎች ውስጥ የተወሰኑት...

የኢሰመኮ ዓመታዊ የሰብዓዊ መብቶች ሪፖርት አሳሳቢ ያላቸው ጥሰቶች ምንድናቸው?

በሃሚድ አወል የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ባለፉት 12 ወራት ከዚህ በፊት ያልነበሩ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች “መጠናቸው ሰፍቶ” እየታዩ መምጣታቸውን አስታወቀ። በሰብዓዊ መብት ረገድ በበጎ እርምጃ የሚታዩ ሁኔታዎች መኖራቸውን የገለጸው ኮሚሽኑ፤ የሰዎች በህይወት የመኖር መብት፣ ሰላም እና ደህንነት ላይ “ትርጉም ያለው መሻሻል አልታየም” ብሏል። መንግስታዊው የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ተቋም ይህን ያለው፤...

የጠቅላይ ሚኒስትሩ የፓርላማ ውሎ 

በሃሚድ አወል ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አሀመድ ዛሬ ሐሙስ ሰኔ 29፤ 2015 በተወካዮች ምክር ቤት አባላት ለተነሱላቸው ጥያቄ እና አስተያየቶች ምላሽ እና ማብራሪያ ሲሰጡ ውለዋል። በዛሬው ስብሰባ ከተገኙ 327 ፓርላማ አባላት መካከል ሃያ አንዱ፤ የሰላም እና ጸጥታ፣ ኢኮኖሚዊ እና ፖለቲካዊ ጉዳዮችን የተመለከቱ ጥያቄዎችን አቅርበዋል። ከሰሞኑ በፓርላማ ስብሰባዎች ተደጋግሞ የተነሳው፤ በጠቅላይ ሚኒስትሩ...