ሰሞነኛ ጉዳዮች

በአዲስ አበባ ተግባራዊ ሊደረግ የታቀደው የቤት ግብር ማሻሻያ ምን ዝርዝር ይዟል?

በአማኑኤል ይልቃል የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ባወጣው አዲስ የቤት ግብር ማሻሻያ መሰረት የቤት ባለቤቶች የሚጠበቅባቸውን ክፍያ እንዲፈጽሙ፤ በሶስት መቶ ሺህ ገደማ ቤቶች ላይ የግብር ግመታ እያከናወነ መሆኑን አስታወቀ። ቤቶቹን የመለየት እና ግብር የመገመት ሂደት ከተጠናቀቀ በኋላ፤ ኮንዶሚኒየም ቤቶችን ጨምሮ ከዚህ ቀደም የቤት ግብር የማይከፈልባቸው ቤቶች ክፍያ እንዲፈጽሙ እንደሚያደርግ የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ ገልጿል። በአዲስ አበባ ከተማ ያሉ የእነዚህ ቤቶች ባለቤቶች ሊከፍሉ...

የአዲስ አበባ የክፍለ ከተማ እና ወረዳ ምክር ቤቶች መቀመጫ ብዛትን የሚወስነው አዋጅ ምን ይዟል?

በአማኑኤል ይልቃል የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት የክፍለ ከተማ እና ወረዳ ምክር ቤቶች አባላት ብዛት ከ150 እንዳያንስ እና ከ250 እንዳይበልጥ የሚደነግግ አዋጅ አጸደቀ። አዋጁ ከክፍለ...

የብሔራዊ ባንክ ገዢ ሹም ሽር አንደምታው ምንድነው?

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በሀገሪቱ “ጤናማ የፋይናንስ ስርዓት የመገንባት” እና “የተረጋጋ የዋጋና የውጭ ምንዛሪ ተመን የማስፈን” ኃላፊነት በአዋጅ የተጣለበት መንግስታዊ ተቋም ነው። የብሔራዊ ባንክ ገዢ...

ነባሩ የደቡብ ክልል ስያሜውን እና አደረጃጀቱን ለመቀየር የህገ መንግስት ማሻሻያ ሊያደርግ ነው

- የነባሩን ክልል መጠሪያ ወደ “ማዕከላዊ ኢትዮጵያ” ለመቀየር ምክረ ሃሳብ ቀርቧል በአማኑኤል ይልቃል የደቡብ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ክልል ስያሜውን እና አደረጃጀቱን ለመቀየር የሚያስችለውን የህገ መንግስት ማሻሻያ ለማድረግ በዝግጅት ላይ መሆኑ ተገለጸ። የህገ መንግስት ማሻሻያ ለማድረግ የታቀደው፤ በመጪው ጥር ወር ከሚደረግ ህዝበ ውሳኔ በኋላ ይመሰረታል ተብሎ የሚጠበቀው የ“ደቡብ ኢትዮጵያ” ክልል በነባሩ...

የአንጋፋው “የኢትዮጵያ ፖስታ” አዳዲስ ውጥኖች  

የ128 ዓመት የዕድሜ ባለጸጋ የሆነው የኢትዮጵያ ፖስታ አገልግሎት፤ የመንግስትን የልማት ፖሊሲ መሰረት በማድረግ የፖስታ አገልግሎቶችን የማቋቋም እና የማስፋፋት ኃላፊነት ያለበት መንግስታዊ ተቋም ነው። በ2001 ዓ.ም. በተሻሻለው የማቋቋሚያ ደንቡ መሰረት፤ ተቋሙ በመንግስት የልማት ድርጅትነት የሚተዳደር ሆኗል።  ከመጋቢት 2013 ዓ.ም. ወዲህ “የኢትዮጵያ ፖስታ” የሚል አዲስ መለያውን ያስተዋወቀው ድርጅቱ፤ በርካታ የማሻሻያ ስራዎች...

የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል፤ አዲሱ “የወጪ ቅነሳ እና ቁጠባ ስርዓት መመሪያ” ምን አይነት ገደቦችን በውስጡ...

የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልላዊ መንግስት ለ2015 በጀት ዓመት ጥብቅ “የወጪ ቅነሳ እና ቁጠባ ስርዓት መመሪያ” ተግባራዊ ማድረግ መጀመሩን አስታውቋል። በክልሉ መንግስት መስተዳድር ምክር ቤት የዛሬ ሁለት ሳምንት ገደማ የጸደቀው ይህ መመሪያ፤ በደመወዝ አከፋፈል፣ በሰራተኛ ቅጥር፣ ለመንግስት ሰራተኞች በሚሰጥ የትምህርት ዕድል ላይ ብርቱ ቁጥጥር የሚያደርግ ነው።  በዚሁ የክልሉ መመሪያ ላይ፤ የቢሮ ኪራይ፣...

በኢትዮጵያ ተፋላሚ ኃይሎች መካከል ይደረጋል ተብሎ ስለሚጠበቀው ድርድር የአሜሪካ ልዩ ልዑክ ምን አሉ?

በተስፋለም ወልደየስ በሰሜን ኢትዮጵያ ዳግም የተቀሰቀሰውን ውጊያ ለማስቆም ዋነኛ መሰናክል የሆነው፤ በተፋላሚ ወገኖች መካከል የተፈጠረው የመተማመን እጦት መሆኑን የአሜሪካ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ ልዑክ ማይክ ሐመር ተናገሩ። አምባሳደር ማይክ ሐመር ይህን ያሉት የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ጠቅላላ ጉባኤን ለመሳተፍ ከሚገኙበት ኒውዮርክ፤ ዛሬ ማክሰኞ መስከረም 10፤ 2015 በቪዲዮ ኮንፍረስ በሰጡት መግለጫ ነው።  እስካለፈው አርብ...

በጉራጌ ዞን የሚገኙ አራት ወረዳዎች እና አንድ የከተማ አስተዳደር፤ የ“ክላስተር” አደረጃጀትን በየምክር ቤቶቻቸው አጸደቁ

በሃሚድ አወል በደቡብ ክልል ጉራጌ ዞን የሚገኙ አራት ወረዳዎች እና አንድ የከተማ አስተዳደር የ“ክላስተር” አደረጃጀትን ዛሬ ቅዳሜ ነሐሴ 7፤ 2014 በየምክር ቤቶቻቸው ባካሄዱት አስቸኳይ ጉባኤ አጸደቁ። የመስቃን እና የምስራቅ መስቃን ወረዳዎች እንዲሁም የቡታጅራ ከተማ ማዕከሉን ቡታጅራ ያደረገ አዲስ ዞን ለመመስረት በተጨማሪነት የወሰኑ ሲሆን፤ የማረቆ እና ቀቤና ወረዳዎች ደግሞ ወደ ልዩ...

ጋዜጠኛ ታምራት ነገራ የተጠረጠረበት ጉዳይ ምንድነው?

በተስፋለም ወልደየስ ጋዜጠኛ ታምራት ነገራ “ክልሎችን እና የአገር መሪዎችን በማሳነስ ስድብ እና ብጥብጥ እንዲፈጠር በማድረግ” እንዲሁም “አገርን በማሸበር” ወንጀሎች መጠርጠሩን የኦሮሚያ ፖሊስ ኮሚሽን ለፍርድ ቤት አስታወቀ። ጋዜጠኛው የኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት ፕሬዝዳንት አቶ ሽመልስ አብዲሳን “ገተት” በሚል ቃል ጠርቷል በሚልም ተወንጅሏል። የኦሮሚያ ፖሊስ ኮሚሽን ይህን ያስታወቀው፤ ከትላንት በስቲያ ሐሙስ የካቲት 10፤ 2014...

አምስት የፖለቲካ ፓርቲዎች ጠቅላላ ጉባኤያቸውን በአንድ ወር ውስጥ እንዲያካሄዱ የተቀመጠውን ቀነ ገደብ ተቃወሙ

በሃሚድ አወል ሁለት ሀገር አቀፍ እና ሶስት ክልላዊ የፖለቲካ ፓርቲዎች፤ ጠቅላላ ጉባኤያቸውን በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ እንዲያካሄዱ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የተሰጣቸውን ቀነ ገደብ ተቃወሙ። ፓርቲዎቹ ተቃውሟቸውን ያሰሙት፤ ጠቅላላ ጉባኤ ለማካሄድ “አስቻይ ሁኔታዎች የሉም” በሚል ነው።  ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ 26 ሀገር አቀፍ እና ክልላዊ ፓርቲዎች በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ ጠቅላላ ጉባኤያቸውን...

የእስረኞች ፍቺ፣ የሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት እና ሀገራዊ ምክክር – የአምስት የፖለቲካ ፓርቲዎች ዕይታ 

ከሶስት ቀናት በፊት የኢትዮጵያ መንግስት በእስር ላይ የሚገኙ ፖለቲከኞችን ክስ በማቋረጥ እንዲፈቱ ማድረጉ የሰሞኑ አነጋጋሪ ጉዳይ ሆኖ ቀጥሏል። ይህ የመንግስት እርምጃ ይፋ ከሆነበት ካለፈው አርብ ታህሳስ 29 እስከ ዛሬ ማክሰኞ ድረስ ባሉት ተከታታይ ቀናት፤ አምስት የፖለቲካ ፓርቲዎች ተቃውሞ እና ድጋፋቸውን፣ ምክር እና ማሳሰቢያቸውን ለመንግስት እና ለደጋፊዎቻቸው አቅርበዋል።  የፖለቲካ ፓርቲዎቹ ባወጣቿው...

የኢትዮጵያ አገራዊ የምክክር ኮሚሽን ገለልተኝነት ጥያቄ አስነሳ

በሃሚድ አወል አገራዊ ምክክሮችን ለማመቻቸት ይቋቋማል የተባለው የኢትዮጵያ አገራዊ ምክክር ኮሚሽን ገለልተኝነት ላይ ጥያቄዎች ተነሱበት። ጥያቄዎቹ የተነሱት በኮሚሽኑ ማቋቋሚያ አዋጅ ላይ፤ የተወካዮች ምክር ቤት የህግ፣ ፍትህና ዴሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ትላንት ሰኞ ታህሳስ 11፤ 2014 ባካሄደው የሕዝብ ውይይት መድረክ ላይ ነው።  የኮሚሽኑ ገለልተኝነት ላይ ጥያቄ ያነሱት በወይይት መድረኩ ላይ የተገኙ የፖለቲካ...

“ሁሉን አቀፍ እና አካታች ምክክር ያካሄዳል” የተባለው ኮሚሽን ማቋቋሚያ አዋጅ ምን ይዘቶች አሉት?

የስድስተኛው የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት የመክፈቻ ስብሰባቸውን ባለፈው መስከረም ወር ካከናወኑ ወዲህ፤ እስከ ትላንት ድረስ መደበኛ ስብሰባ ያካሄዱት ለሁለት ጊዜያት ብቻ ነው። ምክር ቤቱ በትላንትናው ዕለት ሶስተኛ መደበኛ ስብሰባውን ለማካሄድ አባላቱን ሲጠራ፤ የተደራረቡ ስራዎችን ለማቃለል ያሰበ ይመስል ስድስት አጀንዳዎችን ይዞ ነበር።   ከስድስቱ አጀንዳዎች ሶስቱ፤ ለምክር ቤቱ በቀረቡ ረቂቅ...

አስራ አንደኛው ክልል፤ ከስልጣን ርክክብ ማግስት

በሃሚድ አወል ከሃዋሳ ከተማ እምብርት ራቅ ብሎ በስተምስራቅ አቅጣጫ በሚገኝ የተንጣለለ ቅጽር ግቢ ውስጥ የተንሰራፋው የደቡብ ክልል ምክር ቤት በባንዲራ እና መፈክሮች በተጻፉባቸው ባነሮች አሸብርቋል። የክልሉ ምክር ቤት የምስረታ ጉባኤውን ባካሄደ አንድ ወር ባልሞላ ጊዜ ለጠራው አስቸኳይ ስብሰባ፤ አባላት እና እንግዶች ወደ ግቢው በመግባት ላይ ናቸው። አብዛኞቹ የምክር ቤቱ አባላት...

የአስራ አንደኛው ክልል የውልደት ዋዜማ

በሃሚድ አወል ዛሬ ግንቦት 28 ነው። ነገሮች በታቀደላቸው መልኩ ተከናውነው ቢሆን ኖሮ የዛሬው ዕለት የኢትዮጵያ አስራ አንደኛ ክልል የውልደት ቀን ይሆን ነበር። ዛሬ እንዲደረግ ቀን ተቆርጦለት በነበረው ህዝበ ውሳኔ አስራ አንደኛውን ክልል ለመመስረት የተሰባሰቡት፤ በደቡብ ክልል የሚገኙ አምስት ዞኖች እና አንድ ልዩ ወረዳ ናቸው። ከስድስተኛው ሀገራዊ ምርጫ ጎን ለጎን የሚካሄደው...

በታጣቂዎች ቁጥጥር ስር ወድቃ ነበር የተባለችው የቤኒሻንጉል ወረዳ ሰሞነኛ ክራሞት

በቅድስት ሙላቱ ወጣት ነው። ያለፉትን 23 ዓመታት ያሳለፈው ተወልዶ ባደገባት ዲዛ ከተማ ነው። ይህቺ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ካማሺ ዞን ስር የምትገኝ አነስተኛ ከተማ ቅርብ ጊዜ ድረስ ስሟ በብዙዎች ኢትዮጵያውያን ዘንድ እስከናካቴውም የሚታወቅ አልነበረም። ባለፈው ሚያዝያ ወር አጋማሽ በከተማይቱ እና በአካባቢዋ የተከሰተው ሁነት ግን ከተማይቱን በብዙዎች አፍ እንድትገባ ያደረገ ብቻ...

የባልደራስ የአዲስ አበባ ማኒፌስቶ ምን ይዟል?

በሃሚድ አወል በመጪው ምርጫ በአዲስ አበባ ከተማ ብቻ የሚወዳደረው ባልደራስ ለእውነተኛ ዲሞክራሲ ፓርቲ፤ ለከተማይቱ ያዘጋጃቸውን አበይት የፖሊሲ አቅጣጫዎች የተነተነበትን ሰነድ በትላንትናው ዕለት ይፋ አድርጓል። በ120 ገጾች የተዘጋጀው የከተማይቱ ማኒፌስቶ፤ ፓርቲው ባለፈው መጋቢት ወር ለህዝብ ይፋ ባደረገው የምርጫ ማኒፈስቶ ላይ የተመሰረተ መሆኑ ተገልጿል።  “ይህ የአዲስ አበባ ከተማ ማኒፌስቶ ፓርቲያችን የህዝብ ውክልና ቢያገኝ...

አዲሱን ክልል መፈተን የጀመሩት የወሰን እና አስተዳደር ጥያቄዎች

በቅድስት ሙላቱ የጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ መንግስት ስልጣኑን ከተረከበ ከሶስት ዓመታት ወዲህ በኢትዮጵያ ተደጋግመው ከሚታዩ ፖለቲካዊ ትኩሳቶች መካከል፤ የክልሎች ወሰንና የማንነት ጉዳዮች፣ የመሬት ይገባኛል ጥያቄ እና “በዚህኛውም አሊያም በዚያኛው ክልል መተዳደር እንፈልጋለን” የሚሉ ተደጋጋሚ ድምጾች ይገኙበታል። እኒህን መሰል ጥያቄዎች ከተቋቋመ 10 ወራትን ብቻ ወዳስቆጠረው ወደ አዲሱ የሲዳማ ክልልም መሻገር...