ሰሞነኛ ጉዳዮች
ሶማሌላንድን በተመለከተ በፓርላማ ለቀረቡ ጥያቄዎች፤ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ምላሽ ሳይሰጡ ቀሩ
እስራኤል ለሶማሌላንድ ከሰጠችው የነጻ ሉዓላዊ ሀገርነት እውቅና በኋላ ዛሬ የመጀመሪያውን ስብሰባ ያደረገው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት፤ ኢትዮጵያ ከሶማሌላንድ ጋር የደረሰችው የመግባቢያ ስምምነት “የት ደረሰ?” የሚል ጥያቄ አነሳ። በመደበኛ ስብሰባው ላይ የተገኙት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ዶ/ር ጌዲዮን ጢሞቴዎስም ሆነ ምክትሎቻቸው ከሶማሌላንድ ጋር በተያያዘ ለተነሱ ጥያቄዎች ምላሽ ሳይሰጡ ቀርተዋል።
ኢትዮጵያ እና ሶማሌላንድ የዛሬ ሁለት...
እስራኤል ለሶማሌላንድ የሀገርነት እውቅና መስጠቷ ለኢትዮጵያ ምን አንድምታ ይኖረዋል?
እስራኤል ከትላንት በስቲያ አርብ ለራስ ገዝ አስተዳደሯ ሶማሌላንድ የሰጠችው የነጻ ሉዓላዊ ሀገርነት እውቅና በኢትዮጵያ ላይ የሚኖረውን አንድምታ በተመለከተ ሁለት የፖለቲካ ምሁራን ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” አስተያየታቸውን ሰጥተዋል። የመጀመሪያው ኢትዮጵያ ከአረቡ ዓለም ጋር ባላት ግንኙነት ዙሪያ በርካታ ጥናቶችን በማድረግ የሚታወቁት ፕሮፌሰር አደም ካሚል ሲሆኑ ሁለተኛው ደግሞ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካል ሳይንስ መምህር...
እስራኤል ለሶማሌላንድ እውቅና መስጠቷን ተከትሎ ማን ምን አለ?
ላለፉት 34 ዓመታት ራሷን ከሶማሊያ ነጥላ ነጻ እና ሉዓላዊ ሀገር አድርጋ የምትቆጥረው ሶማሌላንድ፤ ዛሬ ዓርብ ታኅሣሥ 17፤ 2018 የመጀመሪያውን ይፋዊ የሀገርነት እውቅና ከእስራኤል አግኝታለች። እስራኤል ለሶማሌላንድ የነጻ ሀገርነት እውቅና መስጠቷን ተከትሎ የተለያዩ አስተያየቶች እየተሰነዘሩ ነው።
የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ፤ ከሶማሌላንዱ ፕሬዝዳንት አብዲራህማን ሞሐመድ አብዱላሂ ጋር በሞባይል ስልክ የቪዲዮ...
የፌስታል ምርቶችን መጠቀም የሚከለክለው አዋጅ የትግበራ ጊዜ እንዲራዘም ሱፐርማርኬቶች እና አምራቾች ጠየቁ
ለአንድ ጊዜ አገልግሎት የሚሰጡ የፕላስቲክ ምርቶችን (ፌስታል) ከአንድ ወር በኋላ መጠቀም የሚከለክለው አዋጅ የትግበራ ጊዜ እንዲራዘምላቸው ሱፐርማርኬቶች እና አምራቾች ጠየቁ። የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን በበኩሉ አዋጁ ተግባራዊ ከመደረጉ አስቀድሞ የተሰጠው የስድስት ወራት የሽግግር ጊዜ እንደማይራዘም ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” አስታውቋል።
በግንቦት 2017 ዓ.ም በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በሙሉ ድምጽ የጸደቀው ይህ አዋጅ፤ “የደረቅ...
የሚኒስትሮች ምክር ቤት፣ የሰላም ሚኒስቴር እና ሶስት ክልሎች ከተፈናቃዮች የመብት ጥሰት ጋር በተያያዘ ክስ...
“ቅድሚያ ለሰብአዊ መብቶች ኢትዮጵያ” የተሰኘ ድርጅት፤ ዓለም-አቀፋዊ እና ሕገ-መንግስታዊ “ግዴታቸውን እና ኃላፊነታቸውን ባለመወጣት” “በተፈናቃዮች ላይ የሰብአዊ መብት ጥሰቶች እንዲደርሱ አድርገዋል” ያላቸውን የሚኒስትሮች ምክር ቤት፣ የሰላም ሚኒስቴር እና ሶስት ክልሎችን በፍርድ ቤት ከሰሰ። ፍርድ ቤቱ ጉዳዩን ለመመልከት ለነገ አርብ ለታኀሣሥ 17፤ 2018 ቀጠሮ ሰጥቷል።ሀገር በቀል የሰብአዊ መብት ተሟጋች ድርጅቱ የክስ...
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መምህራን የመስከረም የደመወዝ ጭማሪ እስካሁንም አለመፈጸሙን በመግለጽ ቅሬታ አቀረቡ
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መምህራን፤ በአዲሱ የደመወዝ ማስተካከያ ጭማሪ መሰረት “የመስከረም ወር ክፍያ አልተፈጸመልንም” ሲሉ በማህበራቸው አማካኝነት ቅሬታ አቀረቡ። የክልሉ ፋይናንስ ቢሮ በበኩሉ ችግሩ የተፈጠረው በመረጃ ክፍተት ምክንያት ለፌደራል መንግስት የተላከው የገንዘብ መጠን ጥያቄ ከሚፈለገው በማነሱ እንደሆነ ገልጾ፤ ይህንኑ ለመቅረፍ ስራዎችን እያከናወነ መሆኑን አስታውቋል።
ለመንግስት ሰራተኞች ከመስከረም ወር ጀምሮ ተግባራዊ የሚደረግ...
በአሜሪካ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ላይ ድንጋጤ እና ፍርሃት ያስከተለው ውሳኔ
የአሜሪካዊቷ ሚኒስትር ክሪስቲ ኖም ውሳኔ በቦስተን ከተማ ለምትኖረው ኢትዮጵያዊቷ ነርስ *ሜላት ገብረ እግዚያብሔር “መርዶ” ሆኖባታል። የአሜሪካ ዲፓርትመንት ኦፍ ሆምላንድ ሴኪዩሪቲ (Department of Homeland Security) ሚኒስትር የሆኑት ክሪስቲ ከትላንት በስቲያ አርብ ያስተላለፉት ውሳኔ፤ እንደ እርሷ ሁሉ “ጊዜያዊ ከለላ” አግኝተው በአሜሪካ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንን አስደንግጧል።
የ54 ዓመቷ ሚኒስትር የአርብ ዕለት ውሳኔ፤ ሜላትን ጨምሮ...
በጋምቤላ ከተማ የሰዓት እላፊ እንዲታወጅ መንስኤ የሆነው ምንድነው?
ብሔራዊው የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ተቋም የሆነው የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) በጋምቤላ ክልል በተደጋጋሚ የሚከሰቱ ግጭቶች አሳሳቢ መሆናቸውን በተለያየ ጊዜ በሚያወጣቸው መግለጫዎች እና ሪፖርቶች ሲገልጽ ቆይቷል። የኮሚሽኑ የሥራ ኃላፊዎች ከሦስት ሳምንት በፊት በክልሉ የስራ ጉብኝት ባደረጉበት ወቅት፤ ይኸው ጉዳይ ተነስቶ ነበር።
የኢሰመኮ ዋና ኮሚሽነር አቶ ብርሃኑ አዴሎ ከጋምቤላ ክልል ርዕሰ...
ከ15 እስከ 20 በመቶ ተፈታኞችን ለዩኒቨርሲቲ ማሳለፍ ከተቻለ “በጣም ትልቅ” ውጤት መሆኑን የትምህርት ሚኒስትሩ...
የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከሚወስዱ ተማሪዎች መካከል ከ15 እስከ 20 በመቶ ያሉትን ወደ ዩኒቨርሲቲ እንዲያልፉ ማድረግ የሚቻል ከሆነ “በጣም ትልቅ” ውጤት እንደሆነ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ተናገሩ። አንድም ተማሪ ለዩኒቨርሲቲ ማሳለፍ ካልቻሉ እና ጉዳት ከደረሰባቸው ትምህርት ቤቶች መካከል 700 ያህሉ ተለይተው፤ “የክትትል” እና “እገዛ” ስራ ከአንድ ወር በኋላ...
ኢትዮጵያ በቀይ ባህር ጉዳይ ላይ እንዲያሸማግሏት ለአሜሪካ፣ ለቻይና እና ሩሲያ ጥያቄ ማቅረቧን ጠቅላይ ሚኒስትር...
ኢትዮጵያ የቀይ ባህር ጉዳይን በተመለከተ ለአሜሪካ፣ ለቻይና፣ ለሩሲያ እና ለበርካታ ሀገራት “እንዲያሸማግሏት” እና “መፍትሔ እንዲያመጡ” ጥያቄ ማቅረቧን ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ተናገሩ። በቀይ ባህር ምክንያት “ከማንም ጋር የመዋጋት ፍላጎት የለንም” ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ውጊያ ከተነሳ ግን ውጤቱ “ግልጽ” እንደሆነ እና ሀገሪቱን “ማንም እንደማይስቆማት” አስጠንቅቀዋል።
አብይ ይህን ያሉት ዛሬ ማክሰኞ...
በታራሚዎች ላይ “የአማራጭ ቅጣትን” ለመተግበር የሚያስችል የአዋጅ ረቂቅ በቅርቡ ለፓርላማ ሊቀርብ ነው
የፍትሕ ሚኒስቴር በእስር የሚቆዩ ታራሚዎችን ቁጥር “ከፍተኛ በሆነ መንገድ” ለመቀነስ ያስችላል ያለውን “የአማራጭ ቅጣት ስርዓትን” ለመተግበር ረቂቅ አዋጅ ማዘጋጀቱን አስታወቀ። የአዋጁ ረቂቅ በቅርቡ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንደሚቀርብም ሚኒስቴሩ ገልጿል።
መስሪያ ቤቱ ይህን የገለጸው፤ የሚኒስቴሩን የ2018 በጀት ዓመት እቅድ እና የሩብ ዓመት ስራ አፈጻጸም በተገመገመበት መድረክ ላይ ነው። የፊት ለፊት...
ምርጫ ቦርድ ሰባተኛውን ጠቅላላ ምርጫ በግንቦት 24 ለማካሄድ ምክረ ሃሳብ አቀረበ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለሰባተኛ ጊዜ የሚካሄደውን ሀገር አቀፍ ምርጫ፤ በመጪው ግንቦት 24፤ 2018 ለማድረግ ምክረ ሃሳብ አቀረበ። ቦርዱ በምርጫው የሚገኘውን ውጤት ይፋ ለማድረግ፤ በረቂቅ የጊዜ ሰሌዳው ያስቀመጠው ዕለት ሰኔ 3፤ 2018 ነው።
ብሔራዊው ምርጫ ቦርድ የጠቅላላ ምርጫውን ረቂቅ የጊዜ ሰሌዳ አዘጋጅቶ ለውይይት ያቀረበው፤ ከትላንት በስቲያ ሰኞ ጥቅምት 10፤ 2018...
በትንሹ 2 ዓመት ዘግይቶ 3 ቢሊዮን ብር ተጨማሪ ወጪ ያስወጣው የመስኖ ፕሮጀክት
በኦሮሚያ ክልል፣ ባሌ ዞን፣ ደሎ መና ወረዳ የሚገኘው የወልመል ወንዝ መስኖ ልማት ፕሮጀክት፤ ከትላንት በስቲያ ቅዳሜ ጥቅምት 8፤ 2018 ዓ.ም በጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ መመረቁ ይፋ ተደርጓል። ይህ የመስኖ ፕሮጀክት ከታቀደለት ጊዜ በትንሹ ሁለት ዓመት ዘግይቶ እና ቀድሞ ከተያዘለት በተጨማሪ ቢያንስ ሶስት ቢሊዮን ብር ወጪ አስወጥቶ ለምረቃ የበቃ ነው።
ፕሮጀክቱ...
በአዲስ አበባ ዘንድሮ የሚጀመር አዲስ የኮሪደር ልማት እንደሌለ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ተናገሩ
በአዲስ አበባ ከተማ በዚህ ዓመት የሚጀመር አዲስ ኮሪደር ልማት እንደማይኖር የከተማይቱ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ። የከተማይቱ አስተዳደር የወንዞች ዳርቻ ልማት ከኮሪደር ልማት ጎን ለጎን ለመስራት ባለፈው ዓመት ከመረከቡ በፊት፤ ባለፉት አምስት ዓመታት በውጭ እርዳታ እና ዜጎች የተከናወነው ስራ “ሁለት ኪሎ ሜትር ብቻ” እንደነበር ከንቲባዋ ይፋ አድርገዋል።
አዳነች ይህን ይፋ ያደረጉት...
ሙሉ ንግግር፦ ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ በተወካዮች እና ፌዴሬሽን ምክር ቤቶች የጋራ ስብሰባ ላይ...
የተከበሩ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ። የተከበሩ የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ። የተከበራችሁ የህዝብ ተወካዮች እና የፌዴሬሽን ምክር ቤት አባላት። ጥሪ የተደረገላችሁ እንግዶች። ክቡራትና ክቡራን!
የኢፌዲሪ ህገ መንግስት በሚደነግገው መሰረት፤ የሁለቱ ምክር ቤቶች የስራ ዘመን መጀመርን በይፋ ለማብሰር በሚከናወነው የመክፈቻ ስነ ስርዓት ላይ ተገኝቼ ንግግር ለማድረግ በመቻሌ ከፍ ያለ...













































