ዜና
ለምርጫ ቦርድ ሰብሳቢነት በዕጩነት የሚቀርቡ ሁለት ግለሰቦች ማንነት፤ እስከ ህዳር ወር ማብቂያ ባለው ጊዜ...
በተስፋለም ወልደየስ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢን የሚተኩ ዕጩዎችን እንዲመለምል የተቋቋመው ኮሚቴ፤ አጣርቶ የሚለያቸውን ሁለት ዕጩዎች የህዳር ወር ከመጠናቀቁ አስቀድሞ ለጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ እንደሚያቀርብ አስታወቀ። ኮሚቴው ጥቆማዎችን ከመጪው ሰኞ ህዳር 3፤ 2016 ጀምሮ ባሉት ተከታታይ አስር ቀናት እንደሚቀበል ገልጿል።
የዕጩ መልማይ ኮሚቴው ይህን ያስታወቀው፤ የጥቆማ አቀራረብ ሂደቱን አስመልክቶ ዛሬ...
አቶ ሳንዶካን ደበበ የጠቅላይ ሚኒስትር ልዩ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ሆነው ተሾሙ
በተስፋለም ወልደየስ
ላለፈው አንድ ዓመት በፕላን እና ልማት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ሆነው ሲሰሩ የቆዩት አቶ ሳንዶካን ደበበ፤ የጠቅላይ ሚኒስትር ልዩ ጽህፈት ቤት ኃላፊ (chief of staff) ሆነው ተሾሙ። ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ በሚኒስትር ዴኤታ ማዕረግ የልዩ ጽህፈት ቤታቸውን እንዲመሩ አቶ ሳንዶካንን የሾሟቸው፤ ከሶስት ሳምንት በፊት መሆኑን ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው...
በዘንድሮው ዓመት ሁለት ቢሊዮን ዶላር የሚያወጡ ተኪ ምርቶችን በሀገር ውስጥ ለማምረት መታቀዱን የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር...
በተስፋለም ወልደየስ
ኢትዮጵያ በዚህ ዓመት ሁለት ቢሊዮን ዶላር ያህል የሚያወጡ ምርቶችን በሀገር ውስጥ ምርቶች ለመተካት ማቀዷን የኢንዱስትሪ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ታረቀኝ ቡሉልታ ገለጹ። ሀገሪቱ ባለፉት ሶስት ወራት ውስጥ 350 ሚሊዮን ዶላር የሚያወጡ ምርቶችን በሀገር ውስጥ ምርት መተካት መቻሏንም አስታውቀዋል።
በ2013 የተዘጋጀው የኢትዮጵያ የአስር ዓመት የልማት ዕቅድ፤ የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ስትራቴጂ በዋናነት ኤክስፖርት...
የቀድሞው የሀዋሳ ከተማ ከንቲባ በቦሌ አየር ማረፊያ በቁጥጥር ስር ዋሉ
በተስፋለም ወልደየስ
በ“ብልሹ አሰራር” እና “አፈጻጸም ድክመት” ተገምግመው ከስልጣናቸው የተነሱት የቀድሞው የሀዋሳ ከተማ ከንቲባ አቶ ጸጋዬ ቱኬ፤ በዛሬው ዕለት በቁጥጥር ስር ዋሉ። አቶ ጸጋዬ በፌደራል የጸጥታ ኃይሎች የተያዙት፤ ለተወሰኑ ጊዜያት “ተሰውረው ከቆዩበት” አሜሪካ ወደ ኢትዮጵያ ከተመለሱ በኋላ ነው ተብሏል።
አቶ ጸጋዬ ዛሬ ማክሰኞ ጥቅምት 13፤ 2016 ረፋድ አምስት ሰዓት ገደማ በቦሌ...
በኢትዮጵያ ግጭት ዋነኛ አጀንዳ እንዲሆን የሚፈልጉ ግለሰቦች “ተልዕኮ ያላቸው ናቸው” – ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ...
ኢትዮጵያ ውስጥ ያለው ግጭት ዋነኛ አጀንዳ እንዲሆን የሚፈልጉ ግለሰቦች “ተልዕኮ ያላቸው (infiltrator) ናቸው” ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ተናገሩ። በሀገሪቱ ያለውን “ግጭት እና አላስፈላጊ መገዳደል”፤ የመከላከያ እና የፖሊስ ተቋማት “እየተቆጣጠሩት” መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትሩ አስታውቀዋል።
አብይ ይህን ያሉት ባለፈው መስከረም ወር መጀመሪያ በአዳማ ከተማ በተካሄደ የብልጽግና ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮች ስልጠና ላይ...
ለ13 ዓመታት ያልተመለሰው የአየር ትራፊክ ተቆጣጣሪዎች ጥያቄ
በተስፋለም ወልደየስ
ጊዜው ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ወደ ስልጣን የመጡ ሰሞን ነው። አራት ኪሎ ከሚገኘው ጽህፈት ቤታቸው ከገቡ ገና አራተኛ ወራቸው። ወቅቱ መንግስትን እና ገዢውን ፓርቲ የሚመለከቱ፤ ከዚህ ቀደም በአደባባይ የማይደመጡ የተለያዩ የተቃውሞ እና ሞጋች ሀሳቦች እንደ ልብ የሚንሸራሸሩበት ነበር። በዚህ ጊዜ ነበር ባልተለመደ መልኩ በአንድ የመንግስት ቁልፍ ተቋም...
በጃፓን የታተሙ የመማሪያ መጻሕፍት በሶስት ሳምንታት ውስጥ ለትምህርት ቤቶች እንደሚከፋፈሉ ትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ
በተስፋለም ወልደየስ
በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ያለውን የመማሪያ መጻሕፍት እጥረት ለመቅረፍ በውጭ ሀገር ከታተሙ መጻሕፍት ውስጥ 249 ኮንቴየነር የህትመት ወጤቶች ከትላንት በስቲያ ጅቡቲ ወደብ መድረሳቸውን የትምህርት ሚኒስቴር ገለጸ። እነዚህ መጻሕፍት በቀጣዮቹ ሶስት ሳምንታት ለየትምህርት ቤቶቹ በሚሰራጩበት ወቅት፤ አንድ መጽሐፍ ለአራት ተማሪዎች እንዲዳረስ ተደርጎ እንደሚከፋፈሉም አስታውቋል።
በዘንድሮው የትምህርት ዘመን ከቅድመ አንደኛ እስከ ሁለተኛ...
በመብት ተሟጋቾች የተተቸው የሊባኖስ እና የኢትዮጵያ ስምምነት ለፓርላማ ቀረበ
በተስፋለም ወልደየስ
የቤት ሰራተኞች መብት እንዲከበር የሚሟገቱ ግለሰቦች እና ተቋማት ትችት ሲያሰሙበት የቆየው፤ የኢትዮጵያ እና የሊባኖስ መንግስታት የስራ ስምሪት ስምምነት ለፓርላማ ቀረበ። በሁለቱ ሀገራት ስምምነት ላይ ለኢትዮጵያውያን የቤት ሰራተኞች የሚከፈለው ዝቅተኛ ደመወዝ አለመካተቱ በዛሬው የተወካዮች ምክር ቤት ስብሰባ ጥያቄ ተነስቶበታል።
ኢትዮጵያ ከ300 ሺህ እስከ 400 ሺህ የሚገመቱ ዜጎቿ በቤት ሰራተኝነት ተቀጥረው...
በሰሜን ኢትዮጵያው ጦርነት ለሞቱ ኢትዮጵያውያን የፖለቲካ ፓርቲዎች የሀዘን ስነ ስርዓት አከናወኑ
በትግራይ ክልል ከትላንት ቅዳሜ ጥቅምት 3፤ 2016 ጀምሮ የታወጀውን የሀዘን ቀን እና የመርዶ ስነ ስርዓት ተከትሎ፤ በአዲስ አበባ የሚገኙ የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲዎች አባላት እና ፖለቲከኞች በሰሜን ኢትዮጵያው ጦርነት ህይወታቸውን ላጡ ሁሉም ኢትዮጵያውያን የጸሎት እና የጧፍ ማብራት ስነ ስርዓት በዛሬው ዕለት አከናወኑ። በስነ ስርዓቱ ላይ የሰባት ሀገራዊ እና ክልላዊ ፓርቲዎች...
አይ.ኤም.ኤፍ እና ኢትዮጵያ በገንዘብ ድጋፍ ጥያቄ ላይ ከስምምነት ለመድረስ በመጪዎቹ ሳምንታት ሊወያዩ ነው
ኢትዮጵያ ከዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት በጠየቀችው የገንዘብ ድጋፍ ላይ ከስምምነት ለመድረስ በሚያስፈልጉ ማሻሻያዎች ላይ በመጪዎቹ ሳምንታት ውይይት እንደሚደረግ አይ.ኤም.ኤፍ ገለጸ። የዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት ልዑክ ወደ አዲስ አበባ በመጓዝ፤ የኢትዮጵያ መንግስት በጠየቀው ድጋፍ ላይ ውይይት ማድረጉን ተቋሙ ዛሬ ሐሙስ ባወጣው መግለጫ አስታውቋል። የተቋሙ ልዑክ በአዲስ አበባ ቆይታ ያደረገው ከመስከረም 14...
በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን “ወደ ሀገራቸው የሚመለሱበት እና የሚያለሙበት ጊዜ አሁን ነው” – ጠቅላይ ሚኒስትር...
ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ በውጭ ሀገር የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን “ወደ ሀገራቸው የሚመለሱበት እና የሚያለሙበት ጊዜ አሁን ነው” አሉ። ከኢትዮጵያ ውጭ ላሉ ዜጎች የአሁኑ ጊዜ “ወደ ውጭ የሚያስቡበት ሳይሆን ወደ ውስጥ የሚያስቡበት ነው” ሲሉም ተናግረዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህን ያሉት አዲስ አበባ በሚገኘው የሳይንስ ሙዚየም ከትላንት ማክሰኞ መስከረም 29፤ 2016 አንስቶ መታየት የጀመረውን...
የአውሮፓ ህብረት እና ኢትዮጵያ የ650 ሚሊዮን ዮሮ የገንዘብ ድጋፍ ተፈራረሙ
የአውሮፓ ህብረት እና ኢትዮጵያ የ650 ሚሊዮን ዮሮ የባለብዙ ዘርፍ ዓመታዊ መርሃግብር (multi-annual indicative program) የልማት ትብብር ስምምነት በዛሬው ዕለት ተፈራረሙ። የገንዘብ ድጋፉ፤ ለአረንጓዴ ልማት፣ ለሰብዓዊ ልማት፣ ለመልካም አስተዳደር እና ለሰላም ግንባታ ዘርፎች የሚውል መሆኑ ተገልጿል።
የልማት ትብብር ስምምነቱን በአውሮፓ ህብረት በኩል የፈረሙት ትላንት ምሽት አዲስ አበባ የገቡት የህብረቱ የዓለም አቀፍ...
የአውሮፓ ህብረት ለኢትዮጵያ ያገደውን ቀጥተኛ በጀት ለመልቀቅ አሁንም መሟላት የሚገባቸው ጉዳዮች እንዳሉ አስታወቀ
የአውሮፓ ህብረት ለኢትዮጵያ መንግስት መስጠት ያቋረጠውን ቀጥተኛ የበጀት ድጋፍ ለመቀጠል፤ አሁንም መሟላት የሚገባቸው ጉዳዮች እንዳሉ አስታወቀ። ህብረቱ ከኢትዮጵያ ጋር ያለውን ትብብር ወደ ነበረበት ለመመለስ “የደረጃ በደረጃ አካሄድን” እንደሚከተል ገልጿል።
ሃያ ሰባት አባል ሀገራትን በስሩ ያቀፈውን የአውሮፓ ህብረትን አቋም ያሳወቁት፤ የአውሮፓ ህብረት የዓለም አቀፍ አጋርነት ኮሚሽነር ዩታ ኡርፒላይነን ናቸው። ኮሚሽነሯ ከገንዘብ...
ዛሬ ምሽት አዲስ አበባ የሚገቡት የአውሮፓ ህብረት ኮሚሽነር፤ ለኢትዮጵያ የ39 ቢሊዮን ብር የገንዘብ ድጋፍ...
በተስፋለም ወልደየስ
የአውሮፓ ህብረት የዓለም አቀፍ አጋርነት ኮሚሽነር ዩታ ኡርፒላይነን ከነገ ጀምሮ በኢትዮጵያ የሁለት ቀናት ጉብኝት ሊያደርጉ ነው። ኮሚሽነሯ በአዲስ አበባ ቆይታቸው ህብረቱ ለቀጣዮቹ ሶስት ዓመታት ለኢትዮጵያ የሚሰጠውን የ39 ቢሊዮን ብር የገንዘብ ድጋፍ ይፋ ያደርጋሉ ተብሏል።
በጥቅምት 2013 በትግራይ ክልል ውጊያ መቀስቀሱን ተከትሎ የአውሮፓ ህብረት ጦርነቱን በተመለከተ ሲያንጸባርቀው በቆየው ጠንካራ አቋም...
በባቢሌ አካባቢ በመንግስት የጸጥታ ኃይሎች መካከል በነበረ የተኩስ ልውውጥ ስድስት ሰዎች መገደላቸውን ኢሰመኮ ገለጸ
የኦሮሚያ እና ሶማሌ ክልሎችን በሚያዋስነው የባቢሌ አካባቢ፤ በሁለቱ ክልሎች የጸጥታ ኃይሎች መካከል መስከረም 7፤ 2016 ዓ.ም በተደረገ የተኩስ ልውውጥ፤ ቢያንስ ስድስት ሰዎች መገደላቸውን እና በርካታ ሰዎች መቁሰላቸውን የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) አስታወቀ። በተኩስ ልውውጡ ህይወታቸውን ያጡት ሰዎች በቆሎጂ የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች መጠለያ ጣቢያ የሚኖሩ እንደነበሩ ኮሚሽኑ ገልጿል።
መንግስታዊው የሰብዓዊ መብት...