ዜና
ለአደጋ ስጋት ምላሽ ፈንድ የሚውል ገቢ፤ ከግለሰቦች እና ከሰራተኞች ደመወዝ እንዲሰበስብ የሚያስገድደው የአዋጅ ረቂቅ...
በቤርሳቤህ ገብረ
ከሁለት ሳምንት በፊት ለፓርላማ በቀረበው የኢትዮጵያ አደጋ ስጋት ስራ አመራር የአዋጅ ረቂቅ የተካተተው እና “ለአደጋ ስጋት ምላሽ” የሚውል ገንዘብ ከግለሰቦች አንዲሰበሰብ የሚያዝዘው ድንጋጌ ጥያቄ ተነሳበት። የአደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን በበኩሉ ከሰራተኞች ደመወዝ እና ከግለሰቦች የሚጠበቀው መዋጮ መጠን፤ ወደፊት ውይይት ከተካሄደበት በኋላ በሚኒስትሮች ምክር ቤት በሚወጣ ደንብ የሚወሰን መሆኑን...
የአማራ ክልል የሀገራዊ ምክክር የአጀንዳ ማሰባሰብ ሂደት ተጀመረ
በተስፋለም ወልደየስ
በመጪው ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ ከአማራ ክልል የሚቀርቡ አጀንዳዎችን የማሰባሰብ ሂደት፤ ዛሬ ቅዳሜ መጋቢት 27፤ 2017 በባህርዳር ከተማ በይፋ ተጀመረ። የተለያዩ የማህበረሰብ ክፍሎችን ወክለው በባህርዳር ከተማ የተሰባሰቡ ከ4,500 በላይ ተሳታፊዎች፤ ክልሉን በመወከል በሀገር አቀፉ ጉባኤ የሚሳተፉ ተወካዮችን ይመርጣሉ።
በባህርዳር ዩኒቨርስቲ ስቴዲየም በተካሄደው በዛሬው የመክፈቻ ስነ ስርዓት ላይ የተገኙት የማህበረሰብ ክፍሎቹ...
በአማራ ክልል ጃዊ ወረዳ በተከሰተ አተት መሰል ወረርሽኝ የሁለት ሰዎች ህይወት አለፈ
በቤተልሔም ሠለሞን
በአማራ ክልል፣ በአዊ ብሔረሰብ አስተዳደር፣ ጃዊ ወረዳ ከትላንት በስቲያ ሰኞ ጀምሮ በተከሰተ የአጣዳፊ ተቅማጥ እና ትውከት (አተት) መሰል ወረርሽኝ የሁለት ሰዎች ህይወት ማለፉን የወረዳው አስተዳደር ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ገለጸ። በወረዳው በሁለት ቀናት ውስጥ ብቻ በበሽታው የተያዙ ሰዎች ቁጥር 40 ገደማ መድረሱን የወረዳው የጤና ጽህፈት ቤት አስታውቋል።
አተት መሰል ወረርሽኙ መጀመሪያ...
የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር የስልጣን ጊዜ ለማራዘም የሚያስችል የአዋጅ ማሻሻያ በፓርላማ ጸደቀ
በቤርሳቤህ ገብረ
የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ማክሰኞ መጋቢት 23፤ 2017 ባካሄደው መደበኛ ስብሰባ፤ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር የስልጣን ጊዜን ለማራዘም የሚስችል የአዋጅ ማሻሻያ አጸደቀ። የአዋጅ ማሻሻያው በአብላጫ ድምጽ ሲጸድቅ፤ ሁለት የፓርላማ አባላት ድምጽ ከመስጠት ታቅበዋል።
ፓርላማው ማሻሻያውን ያጸደቀለት አዋጅ፤ የፌደራል መንግስት በክልሎች ጣልቃ የሚገባበት ስርዓት ለመደንገግ ከ21 ዓመት በፊት የወጣ...
የክልል ጊዜያዊ አስተዳደርን የቆይታ ጊዜ የማራዘም ስልጣን፤ ለፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ የሚሰጥ የአዋጅ...
በተስፋለም ወልደየስ
የፌደራል መንግስት በክልሎች የሚያቋቁመውን ጊዜያዊ አስተዳደር የስራ ዘመን፤ ለሁለት ጊዜ የማራዘም ስልጣን ለፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ የሚሰጥ የአዋጅ ማሻሻያ በነገው ዕለት ለፓርላማ ሊቀርብ ነው። የአዋጅ ማሻሻያው፤ የአፈ ጉባኤው ውሳኔ በፌዴሬሽን ምክር ቤት መደበኛ ጉባኤ ተቀባይነት ካላገኘ፤ ጊዜያዊ አስተዳደር በተቋቋመበት ክልል “በአራት ወራት ጊዜ ውስጥ” “ምርጫ እንዲደረግ” ያስገድዳል።
ይህ...
ፖሊስ በአራት የኢቢኤስ ቴሌቪዥን ሰራተኞች ላይ የጠየቀው የ14 ቀናት የምርመራ ጊዜ በፍርድ ቤት ተፈቀደለት
⚫ በተጨማሪ አራት የጣቢያው ሰራተኞች ላይ የቀረበው የጊዜ ቀጠሮ ጥያቄ ለነገ ተቀጥሯል
በቤርሳቤህ ገብረ
የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት፤ ፖሊስ “በሽብር ወንጀል ጉዳይ ጠርጥሬያቸዋለሁ” ባላቸው አራት የኢቢኤስ ቴሌቪዥን ጣቢያ ሰራተኞች ላይ የ14 ቀናት የምርመራ የጊዜ ቀጠሮ ፈቀደ። ባለፈው አርብ ፍርድ ቤት ከቀረቡ የጣቢያው ሰራተኞች መካከል፤ የካሜራ ባለሙያ የሆነው አቶ ቶማስ ደመቀ...
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በየሁለት ሳምንት ልዩነት ተከታታይ የውጭ ምንዛሬ ጨረታ ማካሄድ ሊጀምር ነው
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ “በየሁለት ሳምንት” ልዩነት፤ መደበኛ እና “ተከታታይ” የውጭ ምንዛሬ ሽያጭ ጨረታ ማካሄድ” ሊጀምር እንደሆነ አስታወቀ። “የማዕከላዊ ባንኩን የተረጋጋ የውጭ ምንዛሬ ስርዓት ግብ ለማሳካት” የታቀደ ነው የተባለለት ጨረታ፤ ነገ ማክሰኞ መጋቢት 23፤ 2017 ይጀመራል።
በነገው ጨረታ 50 ሚሊዮን ዶላር ለሽያጭ የቀረበ ሲሆን፤ ፍላጎቱ ያላቸው ባንኮች ሰነዶቻቸውን እንዲያስገቡ ብሔራዊ ባንክ...
አምስት የኢቢኤስ ቴሌቪዥን ጣቢያ ሰራተኞች “በሽብር ወንጀል” ተጠርጥረው ፍርድ ቤት ቀረቡ
በቤርሳቤህ ገብረ
የፌደራል ፖሊስ “በሽብር ወንጀል ጉዳይ” ጠርጥሬያቸዋለሁ ያላቸውን አምስት የኢቢኤስ ቴሌቪዥን ጣቢያ ሰራተኞችን በዛሬው ዕለት ፍርድ ቤት አቀረበ። ጉዳዩ የቀረበለት የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት፤ ፖሊስ በጠየቀው የ14 ቀናት የጊዜ ቀጠሮ ላይ ብይን ለመስጠት ለመጪው ሰኞ ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል።
የፌደራል ፖሊስ የጊዜ ቀጠሮውን የጠየቀው፤ በስምንት ተጠርጣሪዎች ላይ እያካሄደ ያለውን የምርመራ ስራ...
ስስ ፌስታል መጠቀምን የሚከለክለው የአዋጅ ማሻሻያ፤ በፓርላማ የህዝብ ውይይት የተፈጻሚነት ጥያቄ ተነሳበት
በቤርሳቤህ ገብረ
ለአንድ ጊዜ ብቻ ጥቅም ላይ የሚውሉ ስስ የፕላስቲክ ከረጢቶችን መጠቀም የሚከለክለው አዲስ የአዋጅ ማሻሻያ፤ በአምራቾች ዘንድ የተፈጻሚነት ጥያቄ ተነሳበት። የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን በበኩሉ፤ የፕላስቲክ ከረጢቶች በሌሎችም የአፍሪካ ሀገራት መታገዳቸውን በመጥቀስ “ወደ ኢትዮጵያ ሲመጣ አዲስ የሚሆንበት ምክንያት የለም” ብሏል።
ስስ የፕላስቲክ ከረጢቶች ክልከላ ጉዳይ ያነጋገረው፤ ዛሬ ረቡዕ መጋቢት 17፤ 2017...
የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት ዕጩዎችን እንዲጠቁም ለትግራይ ህዝብ ጥሪ ቀረበ
ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ፤ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደርን በፕሬዝዳንትነት ለመምራት ብቁ የሚሆኑ ዕጩዎችን እንዲጠቆሙ ለክልሉ ህዝብ ጥሪ አቀረቡ። ዕጩዎቹ “የጊዜያዊ አስተዳደሩን ስራዎች በብቃት የሚያከናውኑ” እንዲሁም “የክልሉን ሰላም እና ደህንነት ማረጋገጥ የሚችሉ መሆን” ይገባቸዋል ተብሏል።ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህን ጥሪ ያቀረቡት፤ ለመላው የትግራይ ህዝብ በይፋዊ የማህበራዊ ትስስር ገጾቻቸው በዛሬው ዕለት ባስተላለፉት መልዕክት...
የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የቀድሞ ታጣቂዎችን ለማቋቋም ያወጣውን “ልዩ መመሪያ” የተፈጻሚነት ጊዜ በድጋሚ ለአንድ ዓመት...
በቤርሳቤህ ገብረ
የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል “በሰላም የተመለሱ” የቀድሞ ታጣቂዎች ለማቋቋም ያወጣውን “ልዩ መመሪያ” ተግባራዊ የሚደረግበትን የጊዜ ወሰን ለተጨማሪ አንድ ዓመት አራዘመ። የመመሪያው የተፈጻሚነት ጊዜ የተራዘመው፤ የተደራጁ የቀድሞ ታጣቂዎች “ድጋፍ ተደርጎላቸው ወደ ስራ እንዲገቡ” እና ቀሪዎቹ “እንዲደራጁ ለማስቻል ነው” ተብሏል።
የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል “የሰላም ተመላሾችን ለማቋቋም” እና “ወደ ስራ ለማስገባት” ያለመ...
የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር የስልጣን ጊዜ ለአንድ ዓመት ሊራዘም እንደሚችል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጥቆማ ሰጡ
የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር የተቋቋመበት “ህግ ተሻሽሎ”፤ የስልጣን ጊዜው ለተጨማሪ አንድ ዓመት ሊራዘም እንደሚችል ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ጥቆማ ሰጡ። የጊዜያዊ አስተዳደሩ ስራ ከተገመገመ በኋላ፤ “በግለሰቦች ደረጃ ለውጥ ሊካሄድ እንደሚችልም” አብይ ተናግረዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህን ያሉት የትግራይ ጉዳይ ወቅታዊ የፖለቲካ ሁኔታን በተመለከተ፤ ከፓርላማ አባላት ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች በሰጡት ምላሽ ነው። ዛሬ...
የታላቁ የህዳሴ ግድብ በስድስት ወራት ውስጥ ሊመረቅ እንደሚችል ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ተናገሩ
የግንባታ ስራው እየተጠናቀቀ እንደሆነ የተነገረለት የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ፤ በስድስት ወራት ውስጥ ሊመረቅ እንደሚችል ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ፍንጭ ሰጡ። በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል፣ በጉባ ወረዳ በመገንባት ላይ የሚገኘው ይኸው ግድብ፤ በአሁኑ ወቅት 74 ቢሊዮን ሜትር ኪዩብ ውሃ መያዙንም አብይ ገልጸዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ስለ ህዳሴው ግድብ የመጠናቀቂያ ጊዜ ፍንጭ የሰጡት፤ አቶ...
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በተከሰተ የእንስሳት በሽታ የሞቱ ከብቶች ብዛት 1,400 ደረሰ
በብርቱካን ዋልተንጉስ
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በሚገኙ አራት ዞኖች ካለፈው ሳምንት መጨረሻ ጀምሮ በተከሰተ የእንስሳት በሽታ ወረርሽኝ፤ ከ1,400 በላይ ከብቶች መሞታቸውን የአካባቢው የስራ ኃላፊዎች ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናገሩ። በክልሉ የሚገኙ 6,500 የሚሆኑ ከብቶች የበሽታው ምልክት እንደታየባቸው የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ግብርና ቢሮ ገልጿል።
ከጋሞ ዞን ወደ ጎፋ፣ ደቡብ ኦሞ እና አሌ ዞኖች የተዛመተው...
ለአደጋ ስጋት ምላሽ ለመስጠት እንዲያስችል ለሚቋቋም ፈንድ፤ የመንግስት እና የግል ተቋማት ገቢ እንዲሰበስቡ የሚያስገድድ...
በቤርሳቤህ ገብረ
የመንግስት እና የግል ተቋማት ከሚሰጧቸው የተለያዩ አገልግሎቶች “ለአደጋ ስጋት ምላሽ ፈንድ” የሚሆን ገቢ እንዲሰበስቡ የሚያስገድድ የአዋጅ ማሻሻያ ለፓርላማ ቀረበ። የሚጠበቅበትን ገቢ ሰብስቦ ወደ ፈንዱ የባንክ ሂሳብ ያላስተላለፈ ድርጅት ወይም ተቋም፤ ከሚጠበቅበት ገንዘብ በተጨማሪ አስር ከመቶ የባንክ ወለድ ቅጣት እንዲከፍል በአዋጁ ይገደዳል።
እነዚህን ግዴታዎች ያካተተው እና ዛሬ ማክሰኞ መጋቢት 9፤...