ዜና

በመቐለ ከተማ የሚገኙ ዳኞች፤ ከደህንነት ስጋት ጋር በተያያዘ ያቀረቧቸው ጥያቄዎች ካልተመለሱ የጀመሩትን የስራ ማቆም እንደሚቀጥሉ ገለጹ

በትግራይ ክልል መቐለ ከተማ የሚገኙ ዳኞች በትላንትናው ዕለት የጀመሩትን የስራ ማቆም ዛሬም በመቀጠላቸው በከተማይቱ የሚገኙ ፍርድ ቤቶች ተዘግተው ዋሉ። ዳኞቹ ለክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር ያቀረቧቸው ጥያቄዎች እስኪፈቱ ድረስ የስራ ማቆማቸውን እንደሚቀጥሉ የትግራይ ዳኞች ማህበር ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ገልጿል።  በመቐለ ከተማ የሚገኙ ዳኞች ስራቸውን ለማቆማቸው በዋነኛነት የጠቀሱት ምክንያት “የደህንነት ችግር አለብን” የሚል ነው። የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር በትላንትናው ዕለት ባወጣው መግለጫም፤ በመቐለ ሰባት...

የውጭ ዜጎች የማይንቀሳቀስ ንብረት ባለቤት እንዲሆኑ የሚያስችላቸው አዋጅ “ጊዜውን የጠበቀ አይደለም” በሚል ተተቸ 

በቤርሳቤህ ገብረ የውጭ ዜጎች በኢትዮጵያ የማይንቀሳቅስ ንብረት ባለቤት እና ባለይዞታ እንዲሆኑ የሚያስችላቸው አዋጅ “ጊዜውን የጠበቀ አይደለም” በሚል በፓርላማ አባላት ተተቸ። ትችቱ የቀረበው ዛሬ ማክሰኞ ግንቦት 12፤...

ውናት በትግራይ እስከ አመጽ ድረስ የሚሄድ የህዝባዊ እምቢተኝነት የፖለቲካ ትግል እንደሚያካሄድ አስታወቀ

በሁለት ጎራ የተከፈሉት የህወሓት ፖለቲከኞች ከብልጽግና ፓርቲም ሆነ ከሻዕቢያ ጋር “የፈጠሩትን ህብረት” እንደማይቀበለው የውድብ ናፅነት ትግራይ (ውናት) ፓርቲ ገለጸ። በክልሉ ህወሓት በብቸኝነት የሚቆጣጠረውን የፖለቲካ...

በኢትዮጵያ የውጭ ዜጎች በሊዝ የመሬት ባለይዞታ እንዲሆኑ የሚፈቅድ የአዋጅ ረቂቅ በነገው ዕለት ለፓርላማ ሊቀርብ...

በተስፋለም ወልደየስየውጭ ዜጎች በኢትዮጵያ መሬትን በሊዝ በባለቤትነት መያዝ የሚያስችላቸው የአዋጅ ረቂቅ፤ በነገው ዕለት ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ሊቀርብ ነው። ኢትዮጵያዊ ዜግነት የሌላቸው ግለሰቦች በኢትዮጵያ መሬትን፣ የመኖሪያ ቤትን ወይም ተያያዥ ግንባታዎችን በባለቤትነት ለመያዝ፤ ቢያንስ 150 ሺህ የአሜሪካ ዶላር ሊመድቡ እንደሚገባ በአዲሱ አዋጅ ተደንግጓል።  የውጭ ዜጎች በኢትዮጵያ የማይንቀሳቀስ ንብረት “ባለቤት” ወይም “ባለይዞታ”...

በፌደራል ደረጃ ካሉ የባለድርሻ አካላት ሀገራዊ የምክክር አጀንዳዎችን የማሰባሰቢያ መድረክ ከአንድ ሳምንት በኋላ ሊካሄድ...

በቤርሳቤህ ገብረ በፌደራል ደረጃ ባሉ የባለድርሻ አካላት የሚደረገው የሀገራዊ ምክክር እና የአጀንዳ ማሰባሰብ መድረክ ከአንድ ሳምንት በኋላ እንደሚካሄድ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ምክትል ዋና ኮሚሽነር ሂሩት ገብረስላሴ ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናገሩ። በዚህ መድረክ ላይ የመከላከያ ሰራዊት አባላት፣ ሀገር አቀፍ የፖለቲካ ፓርቲዎች እና የሲቪል ማህበራት ተወካዮችን ጨምሮ 38 የባለድርሻ አካላት ይሳተፋሉ ተብሏል። ባለፈው...

በኢትዮጵያ በጋዜጠኞች ላይ ስለሚፈጸመው ተደጋጋሚ እስር ሲፒጄ ምን አለ?

በኢትዮጵያ ከመጋቢት ወር አጋማሽ እስከ ሚያዝያ ወር አጋማሽ ባለው አንድ ወር ጊዜ ውስጥ ብቻ 14 ጋዜጠኞች እና የመገናኛ ብዙሃን ተቋማት ሰራተኞች ለእስር ተዳርገው እንደነበር ዓለም አቀፉ የጋዜጠኞች መብት ተሟጋች ድርጅት (ሲፒጄ) አስታወቀ። ከታሰሩት ጋዜጠኞች እና ሰራተኞች ውስጥ ሁለቱ አሁንም በእስር ላይ እንደሚገኙ ሲፒጄ ገልጿል። ሲፔጄ ይህን የገለጸው፤ በየሀገራቱ ያሉ ጋዜጠኞችን...

በሀገራዊ ምክክር ሂደት የሚታየው የምሁራን ተሳትፎ ከሚጠበቀው አንጻር “አነስተኛ ነው” ተባለ 

በቤርሳቤህ ገብረ በኢትዮጵያ ያሉ ምሁራን በሀገራዊ የምክክር ሂደት ላይ ያላቸው ተሳትፎ፤ ሊኖራቸው ከሚገባው “አስተዋጽኦ” አንጻር ሲታይ “አነስተኛ ነው” ሲሉ የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ምክትል ዋና ኮሚሽነር ሂሩት ገብረስላሴ ተናገሩ። አብዛኞቹ ምሁራን ከሂደቱ “ራሳቸውን የማግለል” አሊያም ሁኔታውን “በዝምታ የመመልከት” አካሄዶችን የመከተል “አዝማሚያዎች” እንደሚታይባቸውም ገልጸዋል። ምክትል ዋና ኮሚሽነሯ ይህን የገለጹት፤ በሀገራዊ የምክክር ሂደት ምሁራን...

የአማራ ክልል ዳኞች በፖለቲካ ጉዳዮች ላይ በማንኛውም ማህበራዊ ሚዲያ ላይ “ሃሳብ እንዳይሰጡ” የሚከለክል ደንብ...

በቤርሳቤህ ገብረ በአማራ ክልል የሚገኙ ዳኞች፤ በፖለቲካ፣ በሃይማኖት ወይም “አወዛጋቢ በሆኑ ማህበራዊ ጉዳዮች ላይ “በየትኛውም” ማህበራዊ ሚዲያ “ሃሳብ እንዳይሰጡ” የሚከለክል ደንብ ጸደቀ። ደንቡ በክልሉ የሚገኙ ዳኞች “ሀሰተኛ” ማህበራዊ ሚዲያዎችን “እንዳይጠቀሙ”፣ “እንዳይከተሉ” እና “አባል እንዳይሆኑ” ይከለክላል።  የዳኞች እና የጉባኤ ተሿሚዎችን የስነ-ምግባር እና የዲሲፕሊን የሚመለከተው ይህ ደንብ የጸደቀው ከትላንት በስቲያ ማክሰኞ ግንቦት 5፤...

ህወሓት ከፖለቲካ ፓርቲነት መሰረዙን ምርጫ ቦርድ አስታወቀ  

በተስፋለም ወልደየስ ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) ከትላንት ማክሰኞ ግንቦት 5፤ 2017 ዓ.ም ጀምሮ ከፖለቲካ ፓርቲነት መሰረዙን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አስታወቀ። የምስረታውን የወርቅ ኢዮቤልዮ ባለው የካቲት ወር ያከበረው ህወሓት ከፓርቲነት የተሰረዘው፤ ቦርዱ ያዘዘውን “የእርምት እርምጃ” ተግባራዊ ባለማድረጉ መሆኑን ገልጿል።  ምርጫ ቦርድ ይህን ውሳኔ ያሳለፈው፤ ባለፈው የካቲት ወር መጀመሪያ ለፓርቲው...

አቶ ጌታቸው ረዳ ሶስት ከፍተኛ የትግራይ ሰራዊት አመራሮች “በዘረፋ እና በሰዎች ንግድ ላይ ተሳትፈዋል”...

የቀድሞው የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ፤ ሶስት ከፍተኛ የትግራይ ወታደራዊ አመራሮች “በወርቅ ቁፋሮ እና ንግድ”፣ “የመንግስት ገንዘብ በመዝረፍ” እንዲሁም ”በህገወጥ የሰዎች ዝውውር ላይ ተሳትፈዋል” ሲሉ ወነጀሉ። አቶ ጌታቸው ረዳ ከፋና ቴሌቪዥን ጣቢያ ጋር ባደረጉት ቃለ መጠይቅ በስም ጠቅሰው የወነጀሏቸው ሶስቱ አመራሮች፤ ብርጋዴር ጀነራል ምግበይ ሃይለ፣ ብርጋዴር...

ለጤናው ዘርፍ “ከፍ ያለ” በጀት ለመመደብ ዝግጅቶች እየተደረጉ መሆኑን የጤና ሚኒስትሯ ገለጹ

ለጤናው ዘርፍ በ2018 ዓ.ም. “ከፍ ያለ” በጀት ለመመደብ፤ “በቂ ዝግጅቶች” እየተደረጉ መሆኑን የጤና ሚኒስትሯ ዶ/ር መቅደስ ዳባ ተናገሩ። የዘርፉን በጀት ከፍ ማድረግ ያስፈለገው አሁን ካለው “ወቅታዊ” እና “ነባራዊ” ሁኔታ አንጻር እንደሆነም ሚኒስትሯ ገልጸዋል።  የጤና ሚኒስትሯ ይህን ያሉት ከብሔራዊው ቴሌቪዥን ጣቢያ ጋር ባደረጉት እና ዛሬ ሰኞ ግንቦት 4፤ 2017 በተላለፈው ቃለ...

መንግስት ለመጪው ምርጫ “ሰላማዊ የውድድር ሜዳ እንዲፈጥር” አራት የተቃዋሚ ፓርቲዎች ጥሪ አቀረቡ

በቤተልሔም ሠለሞን በኢትዮጵያ ጠቅላላ ምርጫ ለማካሄድ አንድ ዓመት ከመቅረቱ አኳያ፤ ገዢው ፓርቲ “እውነተኛ” እና “ሁሉን አካታች” የሆነ ድርድር “በአስቸኳይ” በማድረግ እና በሀገር ውስጥ የተፈጠሩ ቀውሶችን በመፍታት፣ “ሰላማዊ የውድድር ሜዳ እንዲፈጥር” አራት የተቃዋሚ ፓርቲዎች ጥሪ አቀረቡ። ፓርቲዎቹ “ለሰላማዊ ትግል ውጤታማነት” እገዛ ለማድረግ፤ መንግስት “የፖለቲካ እስረኞችን” እንዲፈታም ጠይቀዋል። ዛሬ ሰኞ ግንቦት 4፤ 2017...

ዘንድሮ 47 ቢሊዮን ብር የከሰረው ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ፤ በሁለት ዓመት ውስጥ ወደ ትርፋማነት እንደሚሸጋገር የኩባንያው...

ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ በተያዘው ዓመት ኪሳራ ቢያጋጥመውም፤ በሁለት ዓመታት ውስጥ ወደ ትርፋማነት ይሸጋገራል ተብሎ እንደሚጠበቅ የእናት ኩባንያው ኃላፊዎች ተናገሩ። መቀመጫውን በኬንያ ዋና ከተማ ናይሮቢ ያደረገው ሳፋሪኮም ኩባንያ፤ እስከ መጋቢት ወር ባለው የአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ ካገኘው 3 ቢሊዮን ዶላር የአገልግሎት ገቢ 10 በመቶ ገደማ የሚሆነው የኢትዮጵያ ገበያ ድርሻ እንደሆነ አስታውቋል።  ኩባንያው የሚመራበት...

የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር “አላማው ያልታወቀ” ከማንኛውም የውጭ ኃይል ጋር የሚደረግ ግንኙነት “ተቀባይነት የለውም”...

ከማንኛውም የውጭ ኃይል የሚደረግ “አላማው እና ስትራቴጂካዊ ስልቱ ያልታወቀ” ግንኙነት “ተቀባይነት የለውም” ሲል የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ገለጸ። ይህን መሰሉ ግንኙነት፤ የትግራይ ክልልን “መንግስት አልባ የሚያደርግ አደገኛ አካሄድ ነው” ሲልም ጊዜያዊ አስተዳደሩ አቋሙን አስታውቋል። ጊዜያዊ አስተዳደሩ ይህን ያስታወቀው፤ ወቅታዊ ጉዳዮችን በተመለከተ በትግራይ ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ በኩል ዛሬ ከሰዓት ባወጣው መግለጫ...

ኢትዮ ቴሌኮም 40 ተቋማት አገልግሎት መስጠት የጀመሩበትን “የዲጂታል ገበያ” ይፋ አደረገ

በቤርሳቤህ ገብረ መንግስታዊው የቴሌኮም አገልግሎቶች አቅራቢ የሆነው ኢትዮ ቴሌኮም፤ “ዘመን ገበያ” የተሰኘ ሀገር አቀፍ “የዲጂታል ገበያ” መጀመሩን አስታወቀ። የዲጂታል ገበያው በመላው ሀገሪቱ የሚገኙ አምራች እና ነጋዴዎችን፣ ገዢዎችን እና የሎጅስቲክስ ተቋማትን “በቀላሉ ለማገናኘት የሚያስችል ነው”ተብሎለታል።  ኩባንያው የዲጂታል ገበያውን ይፋ ያደረገው፤ ዛሬ ሐሙስ ሚያዝያ 30፣2017 ዓ.ም. አዲስ አበባ በሚገኘው የሳይንስ ሙዚየም ባዘጋጀው መርሃግብር...

የትግራይ የጤና ባለሙያዎች የ17 ወራት ውዝፍ ደመወዝ እንዲከፈላቸው በሰልፍ ጠየቁ

የትግራይ ክልል የጤና ባለሙያዎች በክልሉ በተካሄደው ጦርነት ወቅት ሳያገኙ የቀሩት የ17 ወራት ውዝፍ ደመወዝ እንዲከፈላቸው በሰልፍ ጠየቁ። የጤና ባለሙያዎቹ ምቹ የስራ ሁኔታ እንዲፈጠርላቸውም ጥያቄ አቅርበዋል።  ባለሙያዎቹ ጥያቄያቸውን ያሰሙት፤ ዛሬ ረቡዕ ሚያዝያ 29፤ 2017 ዓ.ም. በመቐለ ከተማ በሚገኙ የተለያዩ የጤና ተቋማት ውስጥ ባካሄዱት ሰላማዊ ሰልፍ ነው። ከዛሬ ጀምሮ ለሶስት ተከታታይ ቀናት በክልሉ...

የኢቢኤስ ቴሌቪዥን እና ሶስት የጣቢያው ሰራተኞች በጥላቻ ንግግር እና ሀሰተኛ መረጃ በማሰራጨት ተከሰሱ 

በተስፋለም ወልደየስ የኢቢኤስ ቴሌቪዥን፣ እህት ኩባንያው እና ሶስት የጣቢያው ሰራተኞች የጥላቻ ንግግር እና ሀሰተኛ መረጃ በማሰራጨት ወንጀል ክስ ቀረበባቸው። በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት በቀረበው በዚህ የክስ መዝገብ ክስ፤ ጋዜጠኛ መዓዛ መሐመድ፣ በኢቢኤስ ቴሌቪዥን “ሀሰተኛ ታሪኳ ተሰራጭቷል” የተባለችው ብርቱካን ተመስገንን ጨምሮ ስድስት ተጠርጣሪዎች በሽብር ወንጀል ተከስሰዋል። በአጠቃላይ 16 ተከሳሾች የተካተቱበትን የክስ መዝገብ፤...

በአምስተኛው ዙር የውጭ ምንዛሬ ጨረታ 60 ሚሊዮን ዶላር ለሽያጭ ማቅረቡን ብሔራዊ ባንክ አስታወቀ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ነገ ረቡዕ በሚያካሄደው የውጭ ምንዛሬ ጨረታ፤ 60 ሚሊዮን ዶላር ለሽያጭ ማቅረቡን አስታወቀ። በጨረታው መሳተፍ የሚፈልጉ ባንኮች የሚያቀርቡትን ዋጋ ነገ ከረፋድ አራት ሰዓት እስከ እኩለ ቀን እንዲያስገቡ ብሔራዊ ባንክ ጥሪ አቅርቧል። ለነገ የታቀደው ጨረታ፤ ኢትዮጵያ የውጭ ምንዛሬ ስርዓት ለውጥ ካደረገች ከሐምሌ 2016 ዓ.ም. ወዲህ አምስተኛ ነው። ብሔራዊ ባንክ...