ዜና
በሰሜን ኢትዮጵያው የግጭት ማቆም ስምምነት አፈጻጸም ላይ ለመወያየት፤ የአሜሪካ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ ልዑክ ወደ...
የኢትዮጵያ መንግስት እና ህወሓት ባለፈው ጥቅምት ወር በተፈራረሙት የግጭት ማቆም ስምምነት አፈጻጸም ላይ ለመነጋገር፤ የአሜሪካ አፍሪካ ቀንድ ልዩ ልዑክ ማይክ ሐመር በድጋሚ ወደ አዲስ አበባ ሊመጡ ነው። ሐመር ይህንን ጉዳይ በተመለከተ ከኢትዮጵያ መንግስት እና ከአፍሪካ ህብረት ባለስልጣናት ጋር በአዲስ አበባ፤ ከትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር አመራሮች ጋር ደግሞ በመቐለ ከተማ...
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የተወሰኑ ተቋማት አገልግሎቶችን ለግል ተቋማት በውክልና አስተላልፎ ሊያሰራ ነው
በአማኑኤል ይልቃል
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ስር ያሉ መስሪያ ቤቶች፤ የተወሰኑ ስራዎቻቸውን በውክልና ለግል ተቋማት አስተላልፈው (outsource) ሊያሰሩ ነው። በዚህ አሰራር ምክንያት ከስራቸው የሚነሱ የከተማ አስተዳደሩ ሰራተኞችን ወደ ሌሎች መስሪያ ቤቶች ለማዘዋወር እና “በሚፈልጉበት የስራ መስክ” እንዲሰማሩ ለመደገፍ መታሰቡም ተገልጿል።
አዲሱን አሰራር ተግባራዊ የማድረግ ሂደትን እየመራ ያለው የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር...
በፊንጫኣ ስኳር ፋብሪካ ላይ ታጣቂዎች ባደረሱት ጥቃት 14 ሰዎች መገደላቸውን የኢትዮጵያ ስኳር ኢንዱስትሪ ግሩፕ...
በአማኑኤል ይልቃል
በኦሮሚያ ክልል ሆሮ ጉድሩ ወለጋ ዞን በሚገኘው ፊንጫኣ ስኳር ፋብሪካ ላይ ታጣቂዎች ባደረሱት ጥቃት፤ 11 የፋብሪካው ሰራተኞች እና ሶስት የአካባቢው ነዋሪዎች እንደተገደሉ ማረጋገጡን የኢትዮጵያ ስኳር ኢንዱስትሪ ግሩፕ ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” አስታወቀ። ፋብሪካው በተፈጸመበት በዚሁ ጥቃት እና ዘረፋ ምክንያት ስራ ማቋሙም ተገልጿል።
ከአዲስ አበባ በ350 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የሚገኘው የፊንጫኣ...
የብልጽግና ፓርቲ የስራ አስፈጻሚ እና ማዕከላዊ ኮሚቴዎች፤ ከመጪው ሰኞ ጀምሮ መደበኛ ስብሰባዎቻቸውን ሊያካሄዱ ነው
በአማኑኤል ይልቃል
የገዢው ብልጽግና ፓርቲ ስራ አስፈጻሚ እና ማዕከላዊ ኮሚቴዎች፤ ከመጪው ሰኞ ግንቦት 21 ጀምሮ ለአንድ ሳምንት ገደማ የሚቆዩ ስብሰባዎችን ሊያካሄዱ ነው። በሁለቱ ኮሚቴዎች መደበኛ ስብሰባዎች፤ ወቅታዊ እና ሀገራዊ ጉዳዮች ይነሳሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ ተነግሯል።
ከመጪው ሰኞ እስከሚቀጥለው ሳምንት ማክሰኞ ዕለት የሚቆዩት የብልጽግና ፓርቲ የስራ አስፈጻሚ እና ማዕከላዊ ኮሚቴዎች መደበኛ ስብሰባዎች፤ የፓርቲው...
ከቃሊቲ ማረሚያ ቤት ለማምለጥ በተደረገ ሙከራ፤ ቢያንስ አምስት ታራሚዎች ቆስለው መያዛቸውን የዓይን እማኞች ተናገሩ ...
በአማኑኤል ይልቃል
በአዲስ አበባ ቃሊቲ ማረሚያ ቤት የሚገኙ የተወሰኑ ታራሚዎች ትላንት ለሊት ለማምለጥ ባደረጉት ሙከራ፤ አንድ እስረኛ ሲገደል ቢያንስ አምስቱ መቁሰላቸውን እና አንዱ ሳያይዝ መቅረቱን የአይን እማኞች እና የአካባቢ ነዋሪዎች ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናገሩ። ከቃሊቲ ማረሚያ ማዕከል የማምለጥ ሙከራ መደረጉን ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ያረጋገጠው የፌደራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን ግን ያመለጠ እስረኛ “የለም”...
በጋምቤላ ክልል ኢታንግ ልዩ ወረዳ በተቀሰቀሰ ግጭት አምስት ሰዎች መገደላቸው ተነገረ
በአማኑኤል ይልቃል
በጋምቤላ ክልል ኢታንግ ልዩ ወረዳ በሁለት ቀበሌዎች ነዋሪዎች መካከል በተከሰተ ግጭት አምስት ሰዎች መገደላቸውን የልዩ ወረዳው አስተዳደር ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” አስታወቀ። በግጭቱ ጉዳት የደረሰባቸው ሰባት ሰዎች ደግሞ በህክምና ላይ መሆናቸውን አስተዳደሩ ገልጿል።
የኑዌር፣ አኝዋ እና ኮሞ ብሔረሰቦች መኖሪያ በሆነው ኢታንግ ልዩ ወረዳ ግጭት የተቀሰቀሰው፤ ባለፈው ሳምንት መጨረሻ እሁድ ግንቦት 13፤...
በ37 የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች በተካሄደ የኦዲት ምርመራ፤ “ምንም ጉድለት” ያልተገኘባቸው ሁለቱ ብቻ መሆናቸው ተገለጸ
በአማኑኤል ይልቃል
የ2013 ሂሳባቸው ኦዲት ከተደረጉ 37 የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች ውስጥ “ምንም ጉድለት ያልተገኘባቸው” ሁለቱ ብቻ እንደሆኑ የትምህርት ሚኒስቴር ገለጸ። ሚኒስቴሩ ኦዲት ከተደረጉት ዩኒቨርስቲዎች ውስጥ 48.6 በመቶው “ተቀባይነት የሚያሳጣ” ደረጃ ላይ እንደሆኑ ተረጋግጧል ብሏል።
የትምህርት ሚኒስቴር ይህንን ያስታወቀው ትላንት ማክሰኞ ግንቦት 15፤ 2015 በተካሄደው የተወካዮች ምክር ቤት መደበኛ ስብሰባ ላይ ነው። በዚህ...
በኢትዮጵያ ካሉ ትምህርት ቤቶች ውስጥ “ከፍተኛ” የሚባለውን ደረጃ ያሟሉ፤ አራት ብቻ መሆናቸውን ትምህርት ሚኒስቴር...
በአማኑኤል ይልቃል
በኢትዮጵያ በአጠቃላይ የትምህርት ዘርፍ ካሉ 47 ሺህ ትምህርት ቤቶች ውስጥ ተፈላጊውን “ከፍተኛ ደረጃ” የሚያሟሉት አራቱ ብቻ መሆናቸውን የትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ። ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድን ጨምሮ ወላጆች፣ የቀድሞ ተማሪዎች እና መምህራንን የሚያሳትፍ፤ የትምህርት ቤቶችን ደረጃ ለማሻሻል ያለመ ሀገር አቀፍ የትምህርት ዘመቻ በአንድ ወር ተኩል ጊዜ ውስጥ ይፋ እንደሚያደርግም ሚኒስቴር...
ለሽያጭ የቀረቡ የመንግስት የስኳር ፋብሪካዎችን ወደ ግል ማዛወር የሚፈልጉ ኩባንያዎች ምክረ ሃሳባቸውን እንዲያቀርቡ ተጠየቁ
የኢትዮጵያ መንግስት በስሩ ያሉ ስምንት የስኳር ፋብሪካዎችን ወደ ግል ማዛወር ለሚሹ ገዢዎች ምክረ ሃሳባቸውን (proposal) እንዲያቀርቡ ጋበዘ። ለሽያጭ ከቀረቡት መካከል የአርጆ ዴዴሳ፣ ከሰም፣ ጣና በለስ እና ተንዳሆ የስኳር ፋብሪካዎች ይገኙበታል።
በመንግስት እጅ ከሚገኙት ከእነዚህ ስምንት ፋብሪካዎች ውስጥ አራቱ በኦሞ ኩራዝ የስኳር ፕሮጀክት ስር የሚገኙ ናቸው። እነዚህን የስኳር ፋብሪካዎች መግዛት የሚሹ...
ባልደራስ ዛሬ ባካሄደው ጠቅላላ ጉባኤ፤ ወደ ሀገር አቀፍ ፓርቲነት ለማደግ የቀረበለትን ውሳኔ አጸደቀ
በአማኑኤል ይልቃል
ባልደራስ ለእውነተኛ ዲሞክራሲ ፓርቲ ወደ ሀገር አቀፍ ፓርቲነት ለማደግ ዛሬ እሁድ ግንቦት 13፤ 2015 ባካሄደው ጠቅላላ ጉባኤ ወሰነ። በዛሬው የጠቅላላ ጉባኤ ስብሰባ፤ ባልደራስን በምክትል ፕሬዝዳንትነት ሲያገለግሉ የቆዩት አቶ አምሃ ዳኘው በፕሬዝዳንትነት ተመርጠዋል።
ባልደራስ ከምስረታ ጉባኤው በኋላ ባካሄደው የዛሬው የመጀመሪያ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ፤ የፓርቲውን የወደፊት አቅጣጫ በሚወስኑ ዋነኛ ጉዳዮች ላይ...
የቡድን ሰባት ሀገራት፤ የኢትዮጵያ መንግስት እና ህወሓት ለፕሪቶሪያ ስምምነት ሙሉ ትግበራ ቁርጠኛ እንዲሆኑ ጥሪ...
የኢትዮጵያ መንግስት እና ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) በደቡብ አፍሪካ ለተፈረመው ግጭት የማቆም ስምምነት ሙሉ ትግበራ ቁርጠኛ እንዲሆኑ የቡድን ሰባት መሪዎች ጉባኤ ጥሪ አቀረበ። በኢንዱስትሪ የበለጸጉት ሰባት አገራት መሪዎች ትላንት ቅዳሜ ግንቦት 12፤ 2015 ባወጡት መግለጫ በፕሪቶሪያ ግጭት የማቆም ስምምነት መፈረሙን ተከትሎ “የተገኙትን መልካም ለውጦች” በአዎንታ እንደሚቀበሉ አስታውቀዋል።
የአሜሪካው ፕሬዝደንት...
በጸጥታ ኃይሎች ተይዞ የነበረው ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ተለቀቀ
ዛሬ ቅዳሜ ምሽት ከመኖሪያ ቤቱ በጸጥታ ኃይሎች ተይዞ የተወሰደው ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ፤ ምሽት አምስት ሰዓት ገደማ መለቀቁን ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናገረ። ተመስገን ለ“ጥያቄ ትፈለጋለህ” በሚል፤ በአዲስ አበባ ሜክሲኮ አደባባይ አካባቢ ወደሚገኘው የፌደራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ቢሮ ተወስዶ ለሁለት ሰዓት ገደማ መቆየቱን ገልጿል።
ተመስገን ከዚህ ቀደም በፍርድ ቤት ነጻ በተባለበት ክስ ጋር...
ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ በጸጥታ ኃይሎች ተይዞ ተወሰደ
ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ዛሬ ቅዳሜ ምሽት ሁለት ሰዓት ገደማ ግንቦት 12፤ 2015 ከመኖሪያ ቤቱ በጸጥታ ኃይሎች ተይዞ መወሰዱን የዓይን እማኞች ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናገሩ። ተመስገንን የወሰዱት በሁለት ፒክ አፕ ተጨነው የመጡ እና የፖሊስ ደንብ ልብስ የለበሱ የጸጥታ ኃይሎች መሆናቸውን ገልጸዋል።
እስከ ምሽት ድረስ ከቅርብ ጓደኞቹ ጋር የነበረው ተመስገን፤ በአዲስ አበባ ጃንሜዳ...
ጠቅላላ ጉባኤውን እንዳያደርግ ተከልክሎ የነበረው ባልደራስ ፓርቲ፤ በመጪው እሁድ ስብሰባውን ሊያካሄድ ነው
በአማኑኤል ይልቃል
ባልደራስ ለእውነተኛ ዲሞክራሲ ፓርቲ፤ ከሁለት ወራት በፊት በክልከላ ሳቢያ ተደናቅፎ የነበረውን የጠቅላላ ጉባኤ ስብሰባውን ከነገ በስቲያ እሁድ ግንቦት 13፤ 2015 ሊያካሄድ ነው። የፓርቲው ጠቅላላ ጉባኤ በድጋሚ እንዳይስተጓጎል፤ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ስብሰባው ከሚደረግበት ሆቴል ጋር ውል የመግባት እና ለአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የማሳወቅ ስራ እንዳከናወነ ተገልጿል።
ከሶስት ዓመት በፊት...
የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን፤ ከህብረተሰቡ የሚቀርቡ የምክክር አጀንዳዎችን ከዛሬ ጀምሮ መቀበል እንደጀመረ አስታወቀ
በአማኑኤል ይልቃል
የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች የሚላኩለትን የምክክር አጀንዳዎች ከዛሬ ጀምሮ መቀበል እንደጀመረ አስታወቀ። ኮሚሽኑ በሀገራዊ ምክክሩ ላይ የሚሳተፉ ግለሰቦችን የመለየት ስራን፤ በአራት ክልሎች እና በአንድ የከተማ አስተዳደር ከሚቀጥለው ሳምንት ጀምሮ እንደሚያከናውንም ገልጿል።
የምክክር ኮሚሽኑ ዛሬ አርብ ግንቦት 11፤ 2015 በጽህፈት ቤቱ በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ፤ ተሳታፊዎችን የመለየት ስራ...