ዜና
በፍርድ ቤት ውሳኔ ለባለቤቶች የሚወሰኑ የቀበሌ ቤቶች እየጨመሩ በመምጣታቸው፤ ጉዳዩ መፍትሔ እንዲፈለግለት ጥያቄ ቀረበ
በአማኑኤል ይልቃል
በደርግ ጊዜ የተወረሱ የቀበሌ ቤቶችን አስመልክቶ ለፍርድ ቤት ለሚቀርቡ አቤቱታዎች እና ለሚሰጡ ውሳኔዎች “መፍትሔ እንዲፈለግ” የአዲስ አበባ ከተማ ቤቶች ልማት እና አስተዳደር ቢሮ ጥያቄ አቀረበ። ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የቀበሌ ቤቶችን በተመለከተ ለፍርድ ቤቶች በሚቀርቡ አቤቱታዎች ምክንያት፤ ቤቶቹ “ከመንግስት እጅ” እየወጡ መሆኑን ቢሮው ገልጿል፡፡
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ቤቶች ልማት...
የትግራይ ክልል መንግስት መስሪያ ቤቶች፤ ለሰራተኞቻቸው ብድር እንዲሰጡ ተፈቀደላቸው
በአማኑኤል ይልቃል
በትግራይ ክልል የሚገኙ የመንግስት ሰራተኞች ደመወዝ እስከሚከፈላቸው ድረስ ከመስሪያ ቤቶቻቸው ብድር እንዲወስዱ ተፈቀደላቸው። የክልሉ መስሪያ ቤቶች ለሰራተኞቻቸው ማቅረብ የሚችሉት ከፍተኛ ብድር፤ አራት ሺህ ብር እንደሆነ ተገልጿል።
የትግራይ ክልል መንግስት ሰራተኞች የመከላከያ ሰራዊት ክልሉን ለቀቆ ከወጣበት ከሰኔ 2013 ዓ.ም አንስቶ፤ ላለፉት 21 ወራት ደመወዝ አልተከፈላቸውም። የፌደራል መንግስት እና ህወሓት በደቡብ...
ህወሓት ከሽብርተኝነት መዝገብ ተሰረዘ
⚫ 61 የፓርላማ አባላት የውሳኔ ሃሳቡን ተቃውመዋል
በሃሚድ አወል
ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) ከሽብርተኝነት መዝገብ መሰረዙን፤ 61 የፓርላማ አባላት ተቃወሙ። አምስት የፓርላማ አባላትም ድምጽ ከመስጠት ታቅበዋል።
የፓርላማ አባላቱ ተቃውሞ እና ድምጸ ተዐቅቦ የተመዘገበው፤ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በህወሓት ላይ አስተላልፎት የነበረውን የሽብርተኝነት ፍረጃ ለመሰረዝ ዛሬ ረቡዕ መጋቢት 13፤ 2015 ባካሄደው “ልዩ...
የተመድ የሰብዓዊ መብቶች ምክር ቤት ያቋቋመው መርማሪ ኮሚሽን፤ የኢትዮጵያ መንግስትን ወቀሰ
በተስፋለም ወልደየስ
በኢትዮጵያ የተፈጸሙ የሰብዓዊ መብቶች ጥሰቶችን ለመመርመር የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰብዓዊ መብቶች ምክር ቤት ያቋቋመው ኮሚሽን፤ የመርማሪ ቡድን ወደ ሀገሪቱ ለመላክ ተደጋጋሚ ጥያቄ ቢያቀርብም “የኢትዮጵያ መንግስት አልፈቀደልኝም” ሲል ወቀሳ አቀረበ። የኢትዮጵያ መንግስት በበኩሉ፤ ኮሚሽኑ “በተቀመጠለት ኃላፊነት መሰረት ገንቢ በሆነ መልኩ አብሮ ለመስራት ዝግጁ አልነበረም” ሲል ተችቷል።
የመርማሪ ኮሚሽኑ ወቀሳ...
የተወካዮች ምክር ቤት፤ ህወሓትን ከአሸባሪነት ለመሰረዝ የሚያስችል “ልዩ ጉባኤ” በነገው ዕለት ሊያካሄድ ነው
በሃሚድ አወል
የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት፤ የህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይን (ህወሓት) ከአሸባሪነት ለመሰረዝ ነገ ረቡዕ መጋቢት 13፤ 2015 “ልዩ ጉባኤ” ሊያካሄድ መሆኑን የ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ምንጮች ገለጹ። ሰባት የፓርላማ አባላት፤ ለነገው ልዩ ጉባኤ “ማንም አባል እንዳይቀር” ከሚል ማሳሰቢያ ጋር ጥሪ እንደተደረገላቸው ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናግረዋል።
እነዚሁ የምክር ቤት አባላት በነገው ዕለት “ልዩ ጉባኤ”...
በአዲስ አበባ ካሉ ሹፌሮች ውስጥ ከግማሽ በላይ የሚሆኑት ከፍጥነት ወሰን በላይ የሚያሽከረክሩ መሆናቸውን አንድ...
በአማኑኤል ይልቃል
በአዲስ አበባ ከተማ ከሚገኙ አሽከርካሪዎች ውስጥ 59 በመቶው ከፍጥነት ወሰን በላይ እንደሚያሽከረክሩ አንድ ጥናት አመለከተ። ከፍጥነት በላይ ማሽከርከር ባለፉት ዓመታት እየጨመረ መምጣቱ አሳሳቢ መሆኑን ጥናቱን ያካሄዱት ባለሙያዎች ገልጸዋል።
ይህ የተገለጸው፤ በአዲስ አበባ ከተማ የመንገድ ደህንነት አደጋ መንስኤዎችን በተመለከተ የተካሄደው የዳሰሳ ጥናት ግኝት ዛሬ ማክሰኞ መጋቢት 12፤ 2015 ይፋ በተደረገበት መርሃ...
በሰሜን ኢትዮጵያው ጦርነት የተፋለሙ ሁሉም ኃይሎች “የጦር ወንጀል” መፈጸማቸውን አሜሪካ ይፋ አደረገች
አሜሪካ፤ በሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት የተሳተፉ ሁሉም ኃይሎች “የጦር ወንጀሎች ፈጽመዋል” የሚል ድምዳሜ ላይ መድረሷን የሀገሪቱ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንከን ተናገሩ። በምዕራብ ትግራይ አካባቢዎች፤ የአማራ ኃይሎች “የዘር ማጽዳት” እና “በሰብዓዊነት ላይ የሚፈጸም ወንጀል” መፈጸማቸውንም ውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ጨምረው አስታውቀዋል።
ብሊንከን የሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነትን በተመለከተ ሀገራቸው የደረሰችበትን መደምደሚያ ያስታወቁት፤ በዓለም...
የአፍሪካ ህብረት፤ መንግስትን እና በኦሮሚያ ክልል የሚንቀሳቀሰውን ታጣቂ ቡድን እንዲያደራድር የፓርላማ አባላት ጠየቁ
በሃሚድ አወል
የአፍሪካ ህብረት፤ በኦሮሚያ ክልል የሚንቀሳቀሰውን “ታጣቂ ኃይል” እና መንግስትን እንዲያደራድር ከኦሮሚያ ክልል የተመረጡ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ጠየቁ። ህብረቱ በክልሉ ለአራት አመታት “የበርካቶችን” ህይወት የቀጠፈውን “ውጊያ” አቅልሎ ማየቱ እንዳሳዘናቸው የፓርላማ አባላቱ ገልጸዋል።
የተወካዮች ምክር ቤት አባላቱ ጥያቄውን ያቀረቡት፤ በኦሮሚያ ክልል ያለውን ሁኔታ አስመልክቶ ዛሬ ሰኞ፤ መጋቢት 11፤ 2015 ለአፍሪካ...
የመንግስት እና የፓርቲ ኃላፊዎች፤ “ጥላቻን እና ግጭትን ከሚያባብሱ ንግግሮች እና ድርጊቶች እንዲቆጠቡ” ገዢው ፓርቲ...
በየደረጃው የሚገኙ የመንግስት እና የፓርቲ ኃላፊዎች፤ “የህዝብን ህብረ ብሔራዊ አንድነት ከሚንዱ፣ ጥላቻን እና ግጭትን ከሚያባብሱ ንግግሮች እና ድርጊቶች እንዲቆጠቡ” ገዢው ብልጽግና ፓርቲ አሳሰበ። የሃይማኖት አባቶች፣ ሚዲያዎች፣ አክቲቪስቶች እና ምሁራንም፤ ያለፉ ቁስሎችን ከሚቀሰቅሱ፣ ጥላቻን ከሚያነግሱ፣ ህዝብ በጥርጣሬ እንዲተያይ ከሚያደርጉ፣ የሀገርን ሰላምና ደህንነት አደጋ ላይ ከሚጥሉ ድርጊቶች እና ንግግሮች እንዲጠበቁ ጥሪ...
በአዲስ አበባ በ“ባጃጅ” ተሽከርካሪዎች ላይ የተጣለው እግድ ከነገ ጀምሮ እንደሚነሳ የከተማው ትራንስፖርት ቢሮ አስታወቀ
በአማኑኤል ይልቃል
የአዲስ አበባ ከተማ ትራንስፖርት ቢሮ በባለ ሶስት እና አራት እግር የ“ባጃጅ” ተሽከርካሪዎች ላይ የተጣለው እግድ ከነገ ቅዳሜ መጋቢት 8፤ 2015 ጀምሮ እንደሚነሳ አስታወቀ። የ“ባጃጅ” ተሽከርካሪዎች በየትኛውም ርቀት ከአምስት ብር በላይ ማስከፈል እንደማይችሉ ቢሮው ገልጿል።
የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ ይህንን ያስታወቀው የባለሶስት እና አራት እግር “ባጃጅ” ተሽከርካሪዎችን አስመልክቶ ዛሬ መጋቢት...
በደቡብ ክልል ኮንሶ ዞን በደረሰ የጎርፍ አደጋ 13 ሰዎች ህይወት አለፈ
በደቡብ ክልል፤ ኮንሶ ዞን ሰገን ዙሪያ ወረዳ ሁለት ቀበሌዎች በደረሰ የጎርፍ አደጋ፤ የ13 ሰዎች ህይወት ማለፉን የዞኑ መንግስት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ ኃላፊ ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናገሩ። የኮሚዩኒኬሽን መምሪያ ኃላፊው አቶ ሰራዊት ዲባባ “ቁጥራቸው በውል የማይታወቅ እንስሳት” በጎርፍ መወሰዳቸውን አክለዋል።
ትናንት ሐሙስ መጋቢት 7፤ 2015 ከቀኑ አስር ሰዓት ገደማ በጣለው ከባድ ዝናብ፤...
በትግራይ ክልል የሚገኙ ዩኒቨርስቲዎች ለሰራተኞቻቸው ደመወዝ መክፈል ሊጀምሩ ነው
በሃሚድ አወል
በትግራይ ክልል የሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች ለሰራተኞቻቸው ደመወዝ ለመክፈል በዝግጅት ላይ እንደሚገኙ አስታወቁ። የገንዘብ ሚኒስቴር ለሰራተኞች ውዝፍ ደመወዝ መክፈያ እና የአንድ ወር የስራ ማስኬጃ በጀት፤ ባለፈው አርብ መጋቢት 1፤ 2015 እንደፈቀደላቸው ዩኒቨርሲቲዎቹ ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናግረዋል።
ተጠሪነታቸው ለፌደራል ትምህርት ሚኒስቴር የሆኑ አራት ዩኒቨርስቲዎች በትግራይ ክልል ይገኛሉ። በሰሜን ኢትዮጵያው ጦርነት ምክንያት የመማር ማስተማር...
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በ“ባጃጅ” ተሽከርካሪዎች ላይ የጣለውን ገደብ እንዲያነሳ ኢሰመኮ ጠየቀ
በአማኑኤል ይልቃል
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በባለ ሶስት እና አራት እግር የ“ባጃጅ” ተሽከርካሪዎች ላይ የጣለውን ገደብ እንዲያነሳ የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ጠየቀ። ኮሚሽኑ፤ የከተማ አስተዳደሩ “ላልተወሰነ ጊዜ የጣለው እግድ ሕገ መንግስታዊ ጥበቃ የተደረገላቸውን መብቶች አደጋ ላይ የጣለ” ነው ብሏል።
ኢሰመኮ በተሽርካሪዎቹ ላይ የተጣለው እግድ እንዲነሳ የጠየቀው ዛሬ ሐሙስ መጋቢት 7፤...
የአዲስ አበባ የክፍለ ከተማ እና ወረዳ ምክር ቤቶች መቀመጫ ብዛትን የሚወስነው አዋጅ ምን ይዟል?
በአማኑኤል ይልቃል
የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት የክፍለ ከተማ እና ወረዳ ምክር ቤቶች አባላት ብዛት ከ150 እንዳያንስ እና ከ250 እንዳይበልጥ የሚደነግግ አዋጅ አጸደቀ። አዋጁ ከክፍለ ከተማ እና ወረዳዎች የህዝብ ቁጥር ብዛት እንዲሁም ከውክልና ጋር የተያያዙ ጥያቄዎች ተነስተውበታል።
የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት፤ የክፍለ ከተማ እና የወረዳ ምክር ቤት የምርጫ ክልል እና...
የፖለቲካ ፓርቲዎች ጠቅላላ ጉባኤን ያስተጓጎሉ የህግ አስፈጻሚ አካላት ላይ ክስ እንዲመሰረት ምርጫ ቦርድ ጠየቀ
በሃሚድ አወል
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ፤ የፖለቲካ ፓርቲዎች ጠቅላላ ጉባኤን ያሰናከሉ የህግ አስፈጻሚ አካላት ላይ ፍትሕ ሚኒስቴር ክስ እንዲመሰርት ጠየቀ። በመንግስት መስሪያ ቤቶች ስር የሚተዳደሩ የስብሰባ ቦታዎች እና አዳራሾች ለፖለቲካ ፓርቲዎች ጠቅላላ ጉባኤ ክፍት እንዲሆኑም ውሳኔ አሳልፏል።
ቦርዱ ይህን ያስታወቀው፤ ከፖለቲካ ፓርቲዎች ጠቅላላ ጉባኤ ጋር በተያያዘ ከሰሞኑ ያጋጠሙ መስተጓጎሎችን በተመለከተ ዛሬ...