ዜና
በቀበና ከተማ የቀሩ የከሰም ስኳር ፋብሪካ ሰራተኞች መንግስት በአፋጣኝ እንዲደርስላቸው ተማጸኑ
ላለፉት ሁለት ሳምንታት በአፋር ክልል ያለ ማቋረጥ የቀጠለው የመሬት መንቀጥቀጥ፤ ብርቱ ሆኖ ከሚሰማባቸው ስፍራዎች አንዱ የቀበና ከተማ ናት። የቀበና ከተማ አብዛኞቹ ነዋሪዎች የከሰም ስኳር ፋብሪካ ሰራተኞች ናቸው።
አርባ ሁለት ሺህ ገደማ ለሆኑ ሰራተኞች የስራ ዕድል የፈጠረው የከሰም ስኳር ፋብሪካ፤ ባለፉት ቀናት በአካባቢው በተከሰተው የመሬት መንቀጥቀጥ ከፍተኛ ጉዳት አጋጥሞታል። የመሬት መንቀጥቀጡ...
በአዋሽ ሰባት ኪሎ ከተማ ትላንት ምሽት ብቻ 30 ገደማ የመሬት መንቀጥቀጥ ንዝረቶች ተሰምተዋል
በመላው ዓለም የሚከሰቱ የመሬት መንቀጥቀጦችን ከስር ከስር እየተከታተሉ በሚመዘግቡ የምርምር ተቋማት ዘንድ ከሰሞኑ ተደጋግሞ የሚጠቀስ አንድ የኢትዮጵያ አካባቢ አለ - አዋሽ። “አዋሽ” በአፋር ክልል የሁለት ከተሞችም መጠሪያ ነው። አዋሽ ሰባት እና አዋሽ አርባ።
ለሰሞኑ የመሬት መንቀጥቀጥ መነሻ ናቸው በሚባሉት የፈንታሌ እና ዶፋን ተራሮች አቅራቢያ የሚገኙት ሁለቱ ከተሞች፤ በሰዓታት አንዳንዴም በደቂቃዎች...
በመሬት መንቀጥቀጥ ከቀያቸው የተፈናቀሉ ነዋሪዎች፤ አስቸኳይ እርዳታ እንዲደረግላቸው ጠየቁ
በአፋር ክልል የመሬት መንቀጥቀጥ በተደጋጋሚ በተከሰተባቸው ስፍራዎች የሚኖሩ ነዋሪዎችን፤ የአደጋ ስጋት ወደሌለባቸው ቦታዎች የማጓጓዝ ስራ ዛሬ ቅዳሜ ታህሳስ 26፤ 2017 በስፋት ሲከናወን ውሏል። ከከሰም የስኳር ፋብሪካ አቅራቢያ በሚገኘው እና በተለምዶ “ቀበና” ተብሎ በሚጠራው አነስተኛ ከተማ ያሉ ነዋሪዎች፤ በዛሬው ዕለት አካባቢውን ለቅቀው እንዲወጡ ተደርገዋል።
ዛሬ ረፋዱን በስፍራው የነበረ አንድ የዓይን እማኝ፤...
በሬክተር ስኬል 5.8 የደረሰ የመሬት መንቀጥቀጥ ዛሬ ለሊት በአፋር ክልል ተከሰተ
በኢትዮጵያ በሬክተር ስኬል 5.8 የተለካ የመሬት መንቀጥቀጥ፤ ከለሊቱ 9:52 መድረሱን የአሜሪካ የጂኦሎጂካል ሰርቬይ መስሪያ ቤት አስታወቀ። ሰሞኑን ሲከሰቱ ከነበሩት የመሬት መንቀጥቀጦች ዘለግ ላሉ ሰከንዶች የቆየው ርዕደ መሬት፤ ንዝረቱ በአዲስ አበባ የተለያዩ አካባቢዎች ተሰምቷል።
የለሊቱ የመሬት መንቀጥቀጥ የተከሰተው በአፋር ክልል መሆኑን የአውሮፓ ሜዲትራንያን ሴይስሞሎጂ ማዕከል (EMSC) ተቋም መረጃ ያሳያል። ርዕደ መሬቱ...
ዛሬ ምሽት በሬክተር ስኬል 5.5 የተመዘገበ ርዕደ መሬት ተከሰተ
በኢትዮጵያ ከሰሞኑ ከተከሰቱት የመሬት መንቀጥቀጦች ከፍተኛ የሆነው እና በሬክተር ስኬል 5.5 የተመዘገበ ርዕደ መሬት ዛሬ አርብ ምሽት መከሰቱን የአሜሪካ እና የአውሮፓ ተቋማት አስታወቁ። የመሬት መንቀጥቀጡ በአፋር ክልል አዋሽ አካባቢ የተከሰተው ከምሽቱ ሁለት ሰዓት ገደማ ነው።ይህ ርዕደ መሬት ከአዋሽ ከተማ 44 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ባለ ስፍራ የደረሰ መሆኑን የአሜሪካ...
የመሬት መንቀጥቀጥ እየተከሰተባቸው ካሉ ስፍራዎች ነዋሪዎችን ማዘዋወር ተጀመረ
በቤርሳቤህ ገብረ
በአፋር ክልል ገቢ ረሱ ዞን ተደጋጋሚ የመሬት መንቀጥቀጥ እየደረሰባቸው ባሉ ሁለት ቀበሌዎች የሚኖሩ አራት ሺህ ገደማ አባወራዎችን፤ “የአደጋ ስጋት ወዳልሆነ ስፍራ” የማዘዋወር ስራ መጀመሩን አንድ የአካባቢው ባለስልጣን ተናገሩ። አደጋውን ሸሽተው ወደ አዋሽ አርባ ከተማ የገቡ ነዋሪዎችን በአንድ ማዕከል ለማሰባሰብ ምዝገባ እየተካሄደ መሆኑንም ገልጸዋል።
በክልሉ በድግግሞሽም ሆነ በመጠን ባለፈው አንድ...
ኢትዮ ቴሌኮም በሚሰጣቸው አገልግሎቶቹ ላይ ያደረገው የዋጋ ጭማሪ፤ በህዝብ ዘንድ “ቁጣን ቀስቅሷል” ተባለ
በቤርሳቤህ ገብረ
መንግስታዊው የቴሌኮም አገልግሎቶች አቅራቢ ኩባንያ የሆነው ኢትዮ ቴሌኮም ካለፈው መስከረም ወር ጀምሮ በአገልግሎቶቹ ላይ ያደረገው የዋጋ ጭማሪ፤ በህዝብ ዘንድ “ቁጣ ጭምር የቀሰቀሰ” እና “አስደንጋጭ ነው” ሲሉ አንድ የገዢው ፓርቲ የፓርላማ አባል ተቹ። የዋጋ ማሻሻያ የተደረገው፤ “ዝቅተኛ የገቢ ምንጭ ያላቸውን የህብረተሰብ ክፍሎችን ባልነካ መልኩ ነው” ሲል ኢትዮ ቴሌኮም ምላሽ...
ትላንት ለሊት በአፋር ክልል በደረሰ የመሬት መንቀጥቀጥ ሳቢያ ከ20 በላይ ቤቶች እና ሱቆች ፈረሱ...
በቤርሳቤህ ገብረ
በአፋር ክልል በትላንትናው ዕለት በደረሰ የመሬት መንቀጥቀጥ ሳቢያ በገቢ ረሱ ዞን፤ ዱለሳ ወረዳ፣ ድሩፉሊ ቀበሌ የሚገኙ ከ20 በላይ ቤቶች እና ሱቆች መፍረሳቸውን የአካባቢው ነዋሪዎች እና የወረዳው አስተዳዳሪ ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናገሩ። የመሬት መንቀጥቀጡ ዛሬም አለመቆሙን የገለጹት ነዋሪዎች፤ “ከፍተኛ ስጋት” ውስጥ መሆናቸውን ገልጸዋል።
በመላው ዓለም የደረሱ የመሬት መንቀጥቀጥ ክስተቶችን የሚመዘግቡ ተቋማት፤ በአዋሽ...
በአዋሽ አካባቢ ዛሬ ምሽት በሬክተር ስኬል 5.0 የደረሰ የመሬት መንቀጥቀጥ ተከሰተ
● በዛሬው ዕለት ብቻ ሰባት የመሬት መንቀጥቀጦች ተመዝግበዋል
በአፋር ክልል አዋሽ አካባቢ ከሰሞኑ ከደረሱት የመሬት መንቀጥቀጥ ክሰተቶች በመጠኑ ከፍተኛ የሆነ ርዕደ መሬት ዛሬ እሁድ ምሽት መከሰቱን የጀርመን የጂኦሳይንስ የምርምር ማዕከል አስታወቀ። በአካባቢው ከምሽቱ 2 ሰዓት ከ10 ላይ የደረሰው የመሬት መንቀጥቀጥ፤ በሬክተር ስኬል 5.0 የደረሰ እንደሆነ የማዕከሉ መረጃ አመልክቷል።
በሬክተር ስኬል የመለኪያ...
በኢትዮጵያ የታገዱ የሰብአዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች ቁጥር አራት ደረሰ
የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን “ከተቋቋሙበት ዓላማ ውጭ ተንቀሳቅሰዋል” ያላቸውን፤ የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ጉባኤ (ኢሰመጉ) እና የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ተሟጋቾች ማዕከልን (EHRDC) ከማንኛውም የስራ እንቅስቃሴ አገደ። ባለስልጣኑ ባለፈው አንድ ሳምንት ጊዜ ውስጥ ያገዳቸው የሰብአዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች ቁጥር አራት ደርሰዋል።
ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ሁለቱን ሀገር በቀል የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ያገደው፤ ከትላንት...
በ84 ኮሌጆች የሚማሩ ተማሪዎች፤ እስከ ጥር ወር መጀመሪያ ወደ ሌሎች የትምህርት ተቋማት እንዲዘዋወሩ ትዕዛዝ...
በቤርሳቤህ ገብረ
የፌደራል የትምህርትና ስልጠና ባለስልጣን፤ 84 የግል ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት እስከ መጪው ጥር ወር መጀመሪያ ድረስ ተማሪዎቻቸውን ፈቃድ ወዳላቸው ተቋማት እንዲያዘዋውሩ ትዕዛዝ አስተላለፈ። ባለስልጣኑ ይህንን ትዕዛዝ የሰጠው፤ በድጋሚ ሳይመዘገቡ ለቀሩ እና በገዛ ፈቃዳቸው ስራቸውን ለማቋረጥ ለወሰኑ ኮሌጆች ነው።
ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ባወጣው “አዲስ ስታንዳርድ” መሰረት፤ የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት...
በኢትዮጵያ የተጎሳቆለ መሬት መጠን ምን ያህል ነው?
የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ማክሰኞ ታህሳስ 15፤ 2017 ባካሄደው መደበኛ ስብሰባው፤ የአረንጓዴ አሻራ እና የተጎሳቆለ መሬት ማገገሚያ ልዩ ፈንድ ማቋቋሚያ እና አስተዳደር አዋጅን በሙሉ ድምጽ አጽድቋል። አዲሱ አዋጅ፤ የፌዴራል መንግስት ከሀገር ውስጥ ገቢ ምንጭ ከሚመድበው ዓመታዊ በጀት ውስጥ ከ0.5 እስከ 1.0 በመቶ ያህል የሚሆነውን ለልዩ ፈንዱ እንዲመድብ ግዴታ ጥሎበታል።
የልዩ...
ከመተሐራ ከተማ አቅራቢያ ዛሬ ምሽት የመሬት መንቀጥቀጥ ተከሰተ
ከመተሐራ ከተማ አቅራቢያ 13 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በሚገኝ ቦታ ዛሬ ሰኞ ምሽት የመሬት መንቀጥቀጥ መከሰቱን የአሜሪካ የጂኦሎጂካል ሰርቬይ መስሪያ ቤት አስታወቀ። ንዝረቱ አዲስ አበባ ድረስ የተሰማው የዛሬው ምሽት ርዕደ መሬት፤ በሬክተር ስኬል 4.9 የተመዘገበ መሆኑን መስሪያ ቤቱ ገልጿል።የዛሬው የመሬት መንቀጥቀጥ ሃያ አራት ሰዓት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ በአካባቢው ለሁለተኛ...
በሐረር ከተማ የታሸጉ 35 የባንክ ቅርንጫፎች አገልግሎት ወደ መስጠት እንዲመለሱ ለሀረሪ ክልል አቤቱታ ቀረበ
በቤርሳቤህ ገብረ
የኢትዮጵያ ባንኮች ማህበር በሐረር ከተማ የታሸጉ 35 የባንክ ቅርንጫፎች ተከፍተው ለህብረተሰቡ አገልግሎት እንዲሰጥ እንዲደረግ ለሀረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቤቱታ አቀረበ። የክልሉ መንግስት ቅርንጫፎቹ የታሸጉት “ግንባታቸው ባላለቁ ህንጻዎች አገልግሎት እየሰጡ በመሆኑ ነው” ቢልም፤ ማህበሩ ግን ከሌሎች የንግድ ድርጅቶች በተለየ መልኩ እርምጃው በእነርሱ ላይ መወሰዱ ለክልሉ የኮሪደር ልማት የተጠየቀው መዋጮ...
የመብቶች እና ዴሞክራሲ ዕድገት ማዕከል የተሰኘው ሀገር በቀል የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅት በድጋሚ ታገደ
በሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን የተጣለበት እገዳ ባለፈው ሳምንት ተነስቶለት የነበረው የመብቶች እና ዴሞክራሲ ዕድገት ማዕከል (ካርድ) በድጋሚ ታገደ። ሀገር በቀሉ የሰብአዊ መብት ድርጅት የታገደው፤ በተሰጠው ማስጠንቀቂያ መሰረት “አሰራሩን ባለማስተካከሉ” እና “ከዚህ ቀደም የፈጸማቸውን ጥፋቶች በመቀጠሉ ነው” ሲል ባለስልጣኑ ወንጅሏል።
ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ፤ እነዚህን እና ሌሎችን ውንጀላዎችን ለድርጅቱ በጻፈው ደብዳቤ ላይ...