ዜና

የኢትዮጵያን የኢኮኖሚ እድገት “ ‘አላየንም፣ አልሰማንም’ አትበሉ” – ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ

ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ በተለያዩ ጊዜያት በሚያደርጓቸው ንግግሮች፤ ዓለም በኢትዮጵያ “እድገት እና ለውጥ ቢደመምም” በርካታ ኢትዮጵያውያን ግን የተሰራውን ስራ “በቅጡ ለመገንዘብ እና ለማድነቅ እንደሚያዳግታቸው” ሲናገሩ ተደምጠዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ትላንት ቅዳሜ ግንቦት 8፤ 2018 በተካሄደ አንድ ሁነት ላይ ባደረጉት ንግግርም ይህንኑ አቋማቸውን ደግመውታል።  አብይ ንግግሩን ያደረጉት፤ በአዲስ አበባ ከተማ የተገነባው የገላን ጉራ ኢንዱስትሪ ፓርክ ምርቃት መርሃ ግብር ላይ ነበር። ጠቅላይ ሚኒስትሩ...

በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በህዝብ ማመላለሻ አውቶብሶች እና ሌሎች ተሽከርካሪዎች ላይ በተፈጸመ ጥቃት ቢያንስ 30 ሰዎች ተገደሉ

በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ወደ ግልገል በለስ ከተማ በመጓዝ ላይ በነበሩ የህዝብ ማመላለሻ አውቶብሶች እና ሌሎች ተሽከርካሪዎች ላይ ትላንት ማክሰኞ ጠዋት ታጣቂዎች ባደረሱት ጥቃት ቢያንስ...

ብልጽግና ፓርቲ በአምስት ክልሎች መንግስት መመስረት የሚያስችል የዕጩዎች ብዛት በብቸኝነት ይዞ መቅረቡን የምርጫ ቦርድ ሰነድ አመለከተ  

የኦሮሚያ፣ አማራ፣ ቤኒሻንጉል ጉሙዝ፣ ጋምቤላ፣ ሐረሪ ክልሎች እና የድሬዳዋ ከተማ መስተዳድር ምክር ቤቶች ካሏቸው መቀመጫዎች መካከል ከግማሽ በላይ ዕጩዎችን ያቀረበው ገዢው ብልጽግና ፓርቲ መሆኑን...

ወደ መቐለ ተጉዞ የነበረው የኢትዮጵያ አየር መንገድ አውሮፕላን፤ ወደ አዲስ አበባ ተመልሶ ያረፈው ለምንድን...

ዛሬ ቅዳሜ ጠዋት ወደ መቐለ በረራ ያደረገ የኢትዮጵያ አየር መንገድ አውሮፕላን፤ በአሉላ አባ ነጋ አየር ማረፊያ በሚገኝ የኮሚኒኬሽን መሳሪያ ብልሽት ምክንያት ወደ አዲስ አበባ ተመልሶ ለማረፍ መገደዱን አንድ የአየር መንገዱ ኃላፊ እና መንገደኞች ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናገሩ። መንገደኞቹ ከሰዓታት ቆይታ በኋላ በዚያው አውሮፕላን መቐለ መድረሳቸውን ገልጸዋል። የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዛሬ እና...

በነዳጅ የሚሰሩ 1,200 አውቶብሶችን ወደ ጋዝ ተጠቃሚነት ለመቀየር 1.4 ቢሊዮን ብር በጀት ያስፈልጋል ተባለ 

በአዲስ አበባ ከተማ የሚገኙ፣ በነዳጅ የሚሰሩ 1,200 የህዝብ ማመለሻ አውቶብሶችን ሞተር፤ በኢትዮጵያ መመረት የጀመረውን የተፈጥሮ ጋዝ እንዲጠቀሙ ለመቀየር 1.4 ቢሊዮን ብር በጀት እንደሚያስፈልግ የከተማይቱ ትራንስፖርት ቢሮ ገለጸ። በመዲናይቱ የሚገኙ አውቶብሶችን ከነዳጅ ወደ ተፈጥሮ ጋዝ ተጠቃሚነት የመቀየር ሙከራ መጀመሩንም ቢሮው አስታውቋል። የቢሮው ኃላፊ አቶ ያብባል አዲስ ይህን ያስታወቁት፤ ዛሬ አርብ ሚያዝያ 30፤...

ገዢው ብልጽግና ፓርቲ ለ64 የፓርላማ መቀመጫዎች ብቻውን ለምርጫ መቅረቡ ታወቀ

ገዢው ብልጽግና ፓርቲ በመጪው ግንቦት መጨረሻ በሚደረገው ምርጫ፣ በአምስት ክልሎች በሚገኙ 64 የምርጫ ክልሎች ብቻውን ለፓርላማ እንደሚወዳደር የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በትላትንናው ዕለት ይፋ ያደረገው ሰነድ አመለከተ። ከእነዚህ የምርጫ ክልሎች ውስጥ አርባ ስድስቱ በኦሮሚያ፣ አስራ አንዱ ደግሞ በአማራ ክልል የሚገኙ ናቸው።  “ምርጫ 2018 - ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” የተመለከተችው የምርጫ ቦርድ ሰነድ፤...

ከዘንድሮ መጠባበቂያ በጀት 205 ቢሊዮን ብር ገደማ የገንዘብ እጥረት ላጋጠማቸው አስፈጻሚ መስሪያ ቤቶች ተሰጠ...

የፌደራል መንግስት ለዘንድሮው በጀት ዓመት ለመጠባበቂያነት ከያዘው 269 ቢሊዮን ብር ውስጥ  76 በመቶውን ያዋለው፤ የበጀት እጥረት ላጋጠማቸው የአስፈጻሚ መስሪያ ቤቶች ፕሮግራሞች እና ተቋማቱ በበጀት ዝግጅት ጊዜያት ላላካተቷቸው ስራዎች መሆኑን የገንዘብ ሚኒስቴር አስታወቀ። ሚኒስቴሩ ባለፉት ዘጠኝ ወራት ለፌደራል መንግስት መስሪያ ቤቶች የከፈለው የገንዘብ መጠን 847.9 ቢሊዮን ብር እንደሆነም ጨምሮ ገልጿል። ይህ የተገለጸው...

በ2012 ዓ.ም የተመረጠው የትግራይ ክልል ምክር ቤት፤ ዶ/ር ደብረጽዮን ገብረሚካኤል ክልሉን እንዲመሩ ሾመ

ከስድስት ዓመት በተካሄደው አወዛጋቢ ምርጫ የተመረጠው የትግራይ ክልል ምክር ቤት፤ ዛሬ ማክሰኞ ሚያዝያ 27፤ 2018 ባደረገው ስብስባ ዶ/ር ደብረጽዮን ገብረሚካኤልን የክልሉ ፕሬዝዳንት አድርጎ ሾመ። በህወሓት ማዕከላዊ ኮሚቴ ውሳኔ ወደ ስራ እንዲመለስ የተደረገው ይኸው ምክር ቤት፤ ወ/ሮ ኪሮስ ሐጎስን አፈ ጉባኤ፣ ወ/ሮ ምህረት በርሀን ደግሞ ምክትል አፈጉባኤ አድርጎ መርጧል። በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ...

በመቐለ ዛሬ ምሽት የቦምብ ፍንዳታ መድረሱን የከተማይቱ ፖሊስ አረጋገጠ

በትግራይ ክልል፣ መቐለ ከተማ፣ ዛሬ ምሽት ሁለት ሰዓት ገደማ የቦምብ ፍንዳታ መከሰቱን የከተማይቱ ፖሊስ ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ገለጸ። ፍንዳታው የደረሰው በትግራይ ክልል ምክር ቤት እና በክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት ጽህፈት ቤት መካከል ባለ ቦታ ላይ እንደሆነ የከተማይቱ ፖሊስ አስታውቋል። ፖሊስ ይህን ከማስታወቁ አስቀድሞ ክስተቱን በተመለከተ በማህበራዊ የትስስር ገጾች የተጋሩ መረጃዎች፤ የቦምብ...

ባንኮች የሚሰጧቸውን ብድሮች ለአምራች ኢንዱስትሪዎች “ፍትሃዊ በሆነ መንገድ” እንዲያከፋፍሉ ግዴታ የሚጥል አዲስ ህግ ሊወጣ...

የመንግስት እና የግል ባንኮች ለተለያዩ ዘርፎች የሚሰጧቸውን ብድሮች፤ ለአምራች ኢንዱስትሪዎችም “ፍትሃዊ በሆነ መንገድ” እንዲያከፋፍሉ ግዴታ የሚጥል አዲስ ህግ አንድ ወር ባልሞላ ጊዜ እንደሚወጣ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ተናገሩ። በሀገሪቱ ያሉ አምራች ኢንዱስትሪዎች ከኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ ጋር በመተባበር፤ ለአፍሪካ ገበያ የሚቀርቡ ምርቶችን ማከፈፈል የሚያስችሉ ኩባንያዎችን “መፍጠር” እንደሚገባቸውም አሳስበዋል።  ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ...

ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ስራ አመራር ቦርድ ዘጠኝ አዲስ አባላት ተሾሙ

ዕለታዊዎቹን “አዲስ ዘመን” እና “ዘ ኢትዮጵያን ሄራልድ” ጋዜጦች የሚያሳትመውን የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት በበላይነት ለሚመራው የስራ አመራር ቦርድ፤ ዘጠኝ አዲስ አባላት በዛሬው ዕለት ተሾሙ። በፕሬስ ድርጅት የስራ አመራር ቦርድ አባልነት ለሶስት ተከታታይ ጊዜያት ተሹመው የነበሩት ዲያቆን ዳንኤል ክብረት፤ በአሁኑ ሹመት ሳይካተቱ ቀርተዋል። የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅትን እንደገና ለማቋቋም በ2011 ዓ.ም የወጣው አዋጅ፤...

ኢትዮጵያ በዓለም የፕሬስ ነጻነት ዝርዝር 148ኛ ደረጃ አገኘች

ድንበር የለሽ የጋዜጠኞች መብት ተሟጋች ድርጅት (RSF) የ180 ሀገራትን የፕሬስ ነጻነት ሁኔታ በሚመዘንበት ዓለም አቀፍ ዝርዝር፤ ኢትዮጵያ 148ኛ ደረጃ አገኘች። የኢትዮጵያ ጎረቤት ኤርትራ ለሶስተኛ ተከታታይ ጊዜ በዝርዝሩ የመጨረሻውን ደረጃ ይዛለች።  ላለፉት 25 ዓመታት ይህን ዝርዝር ሲያወጣ የቆየው የጋዜጠኞች መብት ተሟጋች ድርጅቱ፤ የ2026 የፈረንጆች ዓመት ዝርዝሩን ይፋ ያደረገው ዛሬ ሐሙስ ሚያዝያ...

የፌደራል ፖሊስ በኮንትሮባንድ ንግድ ላይ የመንግስት ባለስልጣናት እንደማይሳተፉ “በተጨባጭ አረጋግጬያለሁ” አለ 

የፌደራል ፖሊስ ኮንትሮባንድን ለመከላከል ባደረጋቸው “ኦፕሬሽኖች”፤ በዚህ የንግድ እንቅስቃሴ ውስጥ የመንግስት ኃላፊዎች ተሳትፎ እና “ኔትወርክ” የሌለበት መሆኑን “በተጨባጭ ማረጋገጡን” ኮሚሽነር ጄነራል ደመላሽ ገብረሚካኤል ተናገሩ። የጸጥታ ተቋሙ የኮንትሮባንድ ዕቃዎችን “የመያዝ አቅሙ” እንዳደገ የገለጹት ኮሚሽነር ጄነራሉ፤ ባለፈው ዘጠኝ ወር ብቻ 20.5 ቢሊዮን ብር ግምት ያላቸው የወጪ እና የገቢ ንግድ ሸቀጦችን “በቁጥጥር...

ለሁለት ሳምንት “በኢ-መደበኛ ማቆያዎች” ተይዞ የቆየው የ“አዲስ ስታንዳርድ” ማኔጂንግ ኤዲተር ከእስር ተለቀቀ    

የ“አዲስ ስታንዳርድ” የበይነ መረብ መገናኛ ብዙሃን ማኔጂንግ ኤዲተር ጋዜጠኛ ሚሊዮን በየነ፤ ከሁለት ሳምንት እስር በኋላ ትላንት ማክሰኞ ሚያዝያ 20፤ 2018 ከሰዓት በኋላ ተፈትቶ ወደ ቤቱ መመለሱን አሳታሚ ድርጅቱ አስታወቀ። ጋዜጠኛው ታስሮ የቆየው በአዲስ አበባ እና ከአዲስ አበባ ውጭ ባሉ ኢ-መደበኛ የማቆያ ስፍራዎች እንደሆነ የመገናኛ ብዙሃኑ ዋና አዘጋጅ ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር”...

በሳይበር ደህንነት ኃላፊዎች እና ሰራተኞች ላይ እስከ 10 ዓመት የሚደርስ የጽኑ እስራት ቅጣትን የያዘ...

የቁልፍ መሰረተ ልማት አገልግሎት “እንዲቋረጥ”፣ “እንዲስተጓጎል”፣ “ተዓማኒነቱን እንዲያጣ” ወይም “ሚስጥራዊነቱ እንዲጋለጥ” የሚያደርግ ወንጀል “ሆን ብሎ” እንዲፈጸም ያደረገ የሳይበር ደህንነት ኃላፊ ወይም ሰራተኛ፤ ከሰባት ዓመት እስከ አስር ዓመት በሚደርስ ጽኑ እስራት እንዲቀጣ የሚያደርግ የአዋጅ ረቂቅ ለፓርላማ ሊቀርብ ነው። ይኸው አዋጅ በቁልፍ መሰረተ ልማቶች ላይ የሚያጋጥሙ የሳይበር ደህንነት ክስተቶችን ለብሔራዊ ድንገተኛ...

የብልጽግና ፓርቲ የፓርላማ ዕጩ የነበሩት የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት በዲያቆን ዳንኤል ክብረት ተተኩ

በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ላይ ብልጽግና ፓርቲን በመወከል በአዲስ አበባ ከተማ ለፓርላማ አባልነት ዕጩ ሆነው ቀርበው የነበሩት የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ሳሙኤል ክፍሌ፤ በጠቅላይ ሚኒስትሩ የማህበራዊ ጉዳዮች አማካሪ ዲያቆን ዳንኤል ክብረት ተተኩ። ዶ/ር ሳሙኤል ከምርጫው ራሳቸውን ያገለሉት “በግል ምክንያት” እንደሆነ ለ“ምርጫ 2018 - ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናግረዋል። ዶ/ር ሳሙኤል ገዢው ፓርቲ...

የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን አራት አዳዲስ ኮሚሽነሮች ተሾሙለት 

ብሔራዊው የሰብአዊ መብት ተሟጋች ተቋም የሆነው የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) በተጓደሉ ኮሚሽነሮች ምትክ አራት አዳዲስ አመራሮች ተሾሙለት። ዛሬ በፓርላማ ሹመታቸው ከደጸቀላቸው ኮሚሽነሮች መካከል ሶስቱ በተቋሙ እያገለገሉ የቆዩ ናቸው።  በ2012 ዓ.ም የተሻሻለው የኮሚሽኑ ማቋቋሚያ አዋጅ፤ ተቋሙ አንድ ዋና ኮሚሽነር እና አንድ ምክትል ዋና ኮሚሽነር እንዲሁም የሕጻናትና የሴቶች ጉዳዮችን በበላይነት የሚመሩ...

የአውሮፕላን መንገደኞች የአቪዬሽን ደህንነት ክፍያ እንዲከፍሉ የሚያስገድደው አዋጅ ጸደቀ

የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ማክሰኞ ሚያዝያ 13፤ 2018 ባካሄደው መደበኛ ስብሰባ፤ የአውሮፕላን መንገደኞች የአቪዬሽን ደህንነት ክፍያ እንዲከፍሉ የሚያስገድደውን አዋጅ በሁለት ተቃውሞ እና በሁለት ድምጸ ተዓቅቦ በአብላጫ ድምጽ አጸደቀ። ለብሔራዊ መረጃ እና ደህንነት አገልግሎት ገቢ ይደረጋል የተባለው ይህ ክፍያ፤ በፓርላማ አባላት ጥያቄ ተነስቶበታል። የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) የፓርላማ ተመራጩ ዶ/ር...