ዜና
የአዲስ አበባ ከተማ ሰበር ሰሚ ችሎት የጋዜጠኛ ተስፋለም ወልደየስ የዋስትና መብት እንዲከበር አዘዘ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሰበር ሰሚ ችሎት የ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” የበይነመረብ ሚዲያ መሥራች እና ዋና አዘጋጅ ጋዜጠኛ ተስፋለም ወልደየስ የዋስትና መብት ላይ ፖሊስ ያቀረበው አቤቱታ ላይ ውሳኔ አስተላለፏል። የሰበር ሰሚ ችሎቱ የፖሊስን ማመልከቻ ጭብጥ ከመመልከቱ በፊት የቀረበለት ጉዳይ “ይግባኝ ያስቀርባል” ወይስ “አያስቀርብም” የሚለውን ዛሬ ጠዋት መርምሯል። በዚህም ሰበር ሰሚ ችሎቱ ባሳለፈው ውሳኔ...
Ethiopia Insider Editor-in-Chief Tesfalem Waldyes remains in custody despite being granted bail by court.
The Addis Ababa City Court of Appeal today, June 11, 2025, upheld the bail granted to Tesfalem Waldyes, founder and editor-in-chief of the “Ethiopia Insider” online media outlet. However, Tesfalem Waldyes has not been released as of the time of this statement, as the investigating police decided to appeal...
ጋዜጠኛ ተስፋለም ወልደየስን በተመለከተ ከሐቅ ሚዲያና ኮሚኒኬሽን የተሰጠ መግለጫ – ሰኔ 4
የአዲስ አበባ ከተማ ይግባኝ ሰሚ ፍርድ ቤት ዛሬ ሰኔ 4 ቀን፤ 2017 የ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” የበይነመረብ ሚዲያ መሥራች እና ዋና አዘጋጅ ጋዜጠኛ ተስፋለም ወልደየስ በሥር ፍርድ ቤት የተወሰነለትን የዋስትና መብት አጽንቷል። ይሁንና መርማሪ ፖሊስ ለሰበር ሰሚ ችሎት ይግባኝ በመጠየቁ ተስፋለም ወልደየስ ይህ መግለጫ እስከ ወጣበት ሰዓት ድረስ ከእስር አልተፈታም። በአዲስ አበባ ከተማ...
Statement from Haq Media and Communication regarding the arrest of journalist Tesfalem Waldyes
Tesfalem Waldyes, the founder and editor-in-chief of Ethiopia Insider, an online media outlet managed by Haq Media and Communication, was arrested by security forces on Sunday, June 8, 2025. Haq Media and Communications has learned that he was taken into custody by plainclothed officers at the Ghion Hotel in...
የጋዜጠኛ ተስፋለም ወልደየስ መታሰርን በተመለከተ ከሐቅ ሚዲያና ኮሚኒኬሽን የተሰጠ መግለጫ
በሐቅ ሚዲያና ኮሚኒኬሽን ሥር የሚተዳደረው “ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” የበይነመረብ ሚዲያ መሥራች እና ዋና አዘጋጅ ጋዜጠኛ ተስፋለም ወልደየስ እሁድ ሰኔ 1 ቀን፤ 2017 በጸጥታ ኃይሎች በቁጥጥር ሥር ውሏል። በአዲስ አበባ ከሚገኘው ግዮን ሆቴል ቅጥር ግቢ ውስጥ ሲቪል በለበሱ የፀጥታ ኃይሎች በቁጥጥር ሥር የዋለው ተስፋለም ሌሊቱን እስጢፋኖስ አካባቢ በሚገኝ የፖሊስ መምሪያ ሕንፃ...
በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ቡለን ከተማ በተፈጸመ ጥቃት ቢያንስ 10 ሰዎች መገደላቸውን ነዋሪዎች ተናገሩ
በቤርሳቤህ ገብረ
በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል፣ በመተከል ዞን፣ በቡለን ከተማ ዛሬ ንጋት ላይ ታጣቂዎች በፈጸሙት ጥቃት ቢያንስ 10 ሰላማዊ ሰዎች እና የጸጥታ ኃይሎች መገደላቸውን የከተማይቱ ነዋሪዎች ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናገሩ። የመተከል ዞን እና የቡለን ወረዳ አስተዳደር በከተማይቱ ላይ በተፈጸመ ጥቃት የሰዎች ህይወት መጥፋቱን፣ ባንክ ቤትን ጨምሮ በተቋማት ላይ ዝርፊያ እና ጉዳት መድረሱን...
የኢትዮጵያን ድንበር የማካለል ስራ “ተቋማዊ ቅርጽ ሰጥቶ” ለማከናወን በዝግጅት ላይ መሆኑን ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር...
በቤርሳቤህ ገብረ
ኢትዮጵያ ከጎረቤት ሀገራት ጋር የምትዋሰንባቸውን በሺህዎች ኪሎ ሜትር የሚቆጠር ድንበርን “የማካለል ስራ”፤ “ተቋማዊ ቅርጽ ሰጥቶ” ለማከናወን በዝግጅት ላይ መሆኗን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዶ/ር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ አስታወቁ። ሀገሪቱ ካላት ድንበር “በአግባቡ የተሰመረ እና የተለየው” ከ50 በመቶ በታች መሆኑንም ሚኒስትሩ ተናግረዋል።
የድንበር ማካለል ጉዳይ የተነሳው፤ ዛሬ ሐሙስ ግንቦት 28፤ 2017 ዓ.ም...
የ2018 የፌደራል መንግስት በጀት በብር ቢጨምርም፤ በዶላር ስሌት ከፍተኛ ቅናሽ አሳየ
የፌደራል መንግስት ለ2018 ያዘጋጀው በጀት፤ ከዘንድሮው አኳያ በግማሽ ትሪሊዮን ብር ገደማ ዕድገት ቢያሳይም በዶላር ሲሰላ ከፍተኛ ቅናሽ አስመዘገበ። ለሚቀጥለው ዓመት የተዘጋጀው በጀት፤ ሁለት ትሪሊዮን ብር የሚጠጋ እንደሆነ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት አስታውቋል።
በጀቱን የያዘው የአዋጅ ረቂቅ ዛሬ ሐሙስ ግንቦት 28፤ 2017 በተካሄደው የሚኒስትሮች ምክር ቤት መደበኛ ስብሰባ ላይ ቀርቦ ውይይት...
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ከኤርትራ ጋር “የቃላት ጦርነት ውስጥ አልገባንም” አሉ
በቤርሳቤህ ገብረ
በኤርትራ በኩል “ትንኮሳ” ቢኖርም፤ የኢትዮጵያ መንግስት ከሀገሪቱ ጋር “የቃላት ጦርነት ውስጥ አልገባም” ሲሉ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ዶ/ር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ ተናገሩ። ኢትዮጵያ ስትራቴጂክ የሆኑ የሀገራዊ ጥቅም ጉዳዮች ስታነሳ “ትኩሳታቸው የሚጨምሩ ሀገራት አሉ” ያሉት ሚኒስትሩ፤ መንግስት በእነዚህ ጉዳዮች ላይ ያለው አቋም “አይዛነፍም” ሲሉ ለፓርላማ አባላት ገልጸዋል።
ውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ሚኒስትሩ...
የመንግስት እና የግል ሰራተኞች ከደመወዛቸው ላይ ለአደጋ ስጋት ምላሽ ፈንድ እንዲያዋጡ የሚያስገድድ ድንጋጌ ተሰረዘ
በቤርሳቤህ ገብረ
ወደፊት ለሚቋቋመው “የአደጋ ስጋት ምላሽ ፈንድ”፤ ከመንግስት እና ከግል ተቋማት ሰራተኞች ደመወዝ መዋጮ እንዲሰበሰብ የሚያስገድደው የአዋጅ ድንጋጌ ተሰረዘ። ድንጋጌው በዛሬው ዕለት በፓርላማ ከጸደቀው “የአደጋ ስጋት ስራ አመራር አዋጅ” ውስጥ እንዲወጣ የተደረገው፤ በሰራተኞች ላይ “ተደራራቢ ጫና እንዳያስከትል” ታስቦ መሆኑ ተገልጿል።
ባለፈው መጋቢት ወር መጀመሪያ ለተወካዮች ምክር ቤት የቀረበው ይኸው አዋጅ፤...
መጪውን ሀገራዊ ምርጫ “ፈቃጅ” እና “አስቻይ” ሁኔታዎች ባሉባቸው አካባቢዎች ለማድረግ ዝግጅት እያደረገ መሆኑን ምርጫ...
በቤርሳቤህ ገብረ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ፤ መጪው ሀገራዊ ምርጫ “ፈቃጅ” እና “አስቻይ” ሁኔታዎች ባሉባቸው የምርጫ ክልሎች እንደሚደረግ ገለጸ። በሀገሪቱ ያለው የጸጥታ ሁኔታ “በጣም ተለዋዋጭ በመሆኑ”፤ ምርጫው በሚቃረብበት ወቅት ሁኔታው “በዝርዝር” እና “በጥልቀት” የሚታይ መሆኑንም አስታውቋል።
ቦርዱ ይህንን ያስታወቀው፤ የሰባተኛው ሀገራዊ ምርጫ ቅድመ ዝግጅት እና ተያያዥ ጉዳዮችን በተመለከተ ዛሬ ሰኞ ግንቦት 25፤...
የእነ አቶ ጌታቸው ረዳ ፓርቲ በአንድ ወር ከአጋማሽ ውስጥ “በትግራይ መስራች ጉባኤዬን አካሄዳለሁ” አለ
በተስፋለም ወልደየስ
በዚህ ሳምንት መጀመሪያ ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ጊዜያዊ ፍቃድ ያገኘው ዲሞክራሲያዊ ስምረት ትግራይ ፓርቲ (ስምረት)፤ እስከ አንድ ወር ተኩል ባለው ጊዜ ውስጥ መስራች ጉባኤውን እንደሚያካሄድ ገለጸ። ፓርቲው ከመጪው ሰኞ ጀምሮ የአባላት ምልመላ እና ከክልል እስከ ቀበሌ ያሉ አደረጃጀቶችን የመፍጠር ስራዎችን እንደሚያከናውን አስታውቋል።
ስምረት ፓርቲ ይህን የገለጸው፤ ዛሬ ቅዳሜ ግንቦት...
ከ1,700 በላይ “የጥቃቅን ቡድኖች” የምክክር አጀንዳዎችን መሰነዱን ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን አስታወቀ
በተስፋለም ወልደየስ
እስከ ዛሬ ድረስ ባለው ሀገራዊ የምክክር ሂደት፤ ከ200 ሺህ ሰዎች በላይ መሳተፋቸውን ከኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ኮሚሽነሮች አንዱ የሆኑት ዶ/ር አምባዬ ኦጋቶ ተናገሩ። ኮሚሽኑ ከ1,746 በላይ የሆኑ “የጥቃቅን ቡድኖች” የምክክር አጀንዳዎችን መሰነዱንም ኮሚሽነሩ አስታውቀዋል።
ዶ/ር አምባዬ ይህን ያስታወቁት፤ ዛሬ አርብ ግንቦት 22፤ 2017 በአዲስ አበባው ሚሊኒየም አዳራሽ በተጀመረው የፌደራል...
አይ ኤም ኤፍ ለኢትዮጵያ ከሚሰጠው ብድር ውስጥ 260 ሚሊዮን ዶላር ሊለቅ ነው
ኢትዮጵያ እና የዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (አይ ኤም ኤፍ) ባለሙያዎች፤ በተራዘመ የብድር አቅርቦት ሶስተኛ ግምገማ ላይ ከስምምነት ደረሱ። ግምገማው በአይ ኤም ኤፍ ስራ አስፈጻሚ ቦርድ ሲጸድቅ፤ የኢትዮጵያ መንግስት ከዓለም አቀፉ ተቋም ከሚበደረው 3.4 ቢሊዮን ዶላር ውስጥ 260 ሚሊዮን ዶላር ይለቀቅለታል።
የአይ ኤም ኤፍ ቦርድ ግምገማውን ከማጽደቁ በፊት፤ የኢትዮጵያ መንግስት ከይፋዊ...
ለአንድ ሳምንት አገልግሎት አቋርጠው የነበሩት በመቐለ ከተማ የሚገኙ ፍርድ ቤቶች ወደ ስራ ተመለሱ
በዳኞች ስራ ማቆም ምክንያት ለአንድ ሳምንት ያህል ተዘግተው የነበሩ በመቐለ ከተማ የሚገኙ ፍርድ ቤቶች፤ ዛሬ ሐሙስ ስራ ጀመሩ። “የደህንነት ስጋት አለብን” በሚል ምክንያት አገልግሎት መስጠት ያቆሙት በከተማይቱ የሚገኙ ዳኞች ወደ ስራ የተመለሱት፤ ከትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ጋር ውይይት ከተካሄደ በኋላ መሆኑን የትግራይ ዳኞች ማህበር ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ገልጿል።
በመቐለ ከተማ የሚገኙ...