ዜና

በእስር ላይ የሚገኙት የኢሕአፓ አባላት እና የፓርቲው ጠበቃ፤ የ12 ቀናት ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ ተፈቀደባቸው

በሽብር ወንጀል ተጠርጥረው ባለፈው ሰኞ በፖሊስ ቁጥጥር ስር የዋሉት የኢትዮጵያ ሕዝቦች አብዮታዊ ፓርቲ (ኢሕአፓ) አባላት አቶ አበበ አካሉ እና አቶ ይስሀቅ ወልዳይ እንዲሁም የፓርቲው ጠበቃ አቶ አበራ ንጉስ ላይ ፍርድ ቤት የ12 ቀናት ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ ፈቀደ። የምርመራ ጊዜውን የፈቀደው የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት፣ ልደታ ምድብ፣ 1ኛ የጊዜ ቀጠሮ ችሎት ነው። ችሎቱ ለዛሬ ቀጥሮ ተጠርጣሪዎች ባቀረቡት የዋስትና ጥያቄ ላይ ውሳኔ...

የ“አዲስ ስታንዳርድ” ዋና አዘጋጅ ታስሮ መለቀቁን እና የድርጅቱ ንብረቶች በጸጥታ ኃይሎች መወሰዳቸውን አሳታሚው አስታወቀ

የ“አዲስ ስታንዳርድ” የበይነ መረብ መገናኛ ብዙሃን ዋና አዘጋጅ ዮናስ ከድር፤ ባለፈው ቅዳሜ “በጸጥታ አባላት” ተይዞ ከአንድ ቀን በኋላ መለቀቁን አሳታሚ ድርጅቱ አስታወቀ። ይህ ድርጊት...

ፖሊስ ሁለት የኢህአፓ አባላትን እና የፓርቲውን ጠበቃ “የሽብር ጥቃት ለመፈጸም ተንቀሳቅሰዋል” በሚል ወነጀለ   

ከትላንት በስቲያ በፖሊስ ቁጥጥር ስር የዋሉ ሁለት የኢትዮጵያ ሕዝቦች አብዮታዊ ፓርቲ (ኢሕአፓ) አባላት እና የፓርቲው ጠበቃ፤ “የሽብር ጥቃት ለመፈጸም ተንቀሳቅሰዋል” የሚል ውንጀላ ቀረበባቸው። ፖለቲከኞቹ...

የሀገራዊ ምክክር ጉባኤው ከተያዘለት የጊዜ ሰሌዳ በላይ ሊወስድ ይችላል ተባለ

በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ ይጠናቀቃል ተብሎ የነበረው ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ፤ በተያዘለት የጊዜ ሰሌዳ መሰረት እየሄደ አለመሆኑን የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ገለጸ። እስካሁን በጉባኤው የተጠናቀሩ አጀንዳዎች፤ ከሚቀጥለው ሳምንት ሰኞ ጀምሮ 500 ተመካካሪዎችን ለሚይዙ 8 ቡድኖች እንደሚቀርቡ ኮሚሽኑ አስታውቋል።  ከሁለት ሳምንት በፊት ሐምሌ 8፤ 2018 በይፋ የተከፈተው ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ፤...

የአዲስ አበባ ከተማ ጉዳይ በኦሮሚያ ክልል የፖለቲካ ልሂቃን እና በሌሎች ተመካካሪዎች መካከል አለመግባባት ፈጠረ

በአዲስ አበባ ከተማ እየተካሄደ በሚገኘው የሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ላይ ትኩረት ከሳቡ አጀንዳዎች አንዱ የሆነው የአዲስ አበባ ከተማ ጉዳይ፤ በኦሮሚያ ክልል የፖለቲካ ልሂቃን እና በሌሎች ተመካካሪዎች መካከል አለመግባባት ፈጥሯል። “አዲስ አበባ የፌደራል ትሁን ወይስ የኦሮሚያ ክልል አካል?” የሚለው ጥያቄ በጉባኤው ከተደራጁ ጥቃቅን ቡድኖች እስከ ስልታዊ ቡድኖች ድረስ ተንጸባርቋል። ትላንት ረቡዕ ሐምሌ...

የህገ መንግስቱ አንቀጽ 39 ጉዳይ በሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ላይ እያከራከረ ነው

በይፋ ከተከፈተ አንድ ሳምንት ባስቆጠረው ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ ላይ እየተሳተፉ የሚገኙ ተወካዮች፤ በስምንት ዋነኛ አጀንዳዎች በተከፋፈሉ ጉዳዮች ላይ እየተወያዩ ይገኛሉ። ከእነዚህ ዋነኛ አጀንዳዎች መካከል “የመንግስት አደረጃጀት እና ቅርጽ” እንዲሁም “የፖለቲካ ስርዓት፣ የፖለቲካ ውክልና እና የምርጫ ስርዓትን” የሚመለከተው ይገኝበታል። በዚህ አጀንዳ ስር በንዑስ አጀንዳነት ከተያዙ የውይይት ጉዳዮች ውስጥ፤ “የብሔሮች፣ ብሔረሰቦች እና...

ኢትዮ ቴሌኮም በ2018 በጀት ዓመት 215 ቢሊዮን ብር ገቢ ማግኘቱን አስታወቀ

ኢትዮ ቴሌኮም በተጠናቀቀው የ2018 በጀት ዓመት 215.82 ቢሊዮን ብር ገቢ ማግኘቱን አስታወቀ። ገቢው ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የ33.2 በመቶ ዕድገት ያሳየ ነው። መንግስታዊው የቴሌኮም አገልግሎት አቅራቢ ለተመዘገበው ዕድገት እንደ አንድ ምክንያት የጠቀሰው የገቢ ምንጮቹ መስፋፋትን ነው። የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈጻሚ ፍሬህይወት ታምሩ ዛሬ ሐሙስ ሐምሌ 16፤ 2018...

በሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ላይ “ጠንካራ ተቃውሞ” የሚያጋጥማቸው አጀንዳዎች፤ ወደ ህዝበ ውሳኔ ሊመሩ እንደሚችሉ ተገለጸ

በሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ላይ የሚቀርቡ አጀንዳዎች ውሳኔ ላይ የሚደረስባቸው፤ በየደረጃው ያሉ ተሳታፊዎች ከ70 እስከ 75 በመቶ ድጋፍ ሲያገኝ እንደሆነ በኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን የተዘጋጀ ሰነድ አመለከተ። ሁሉንም የውሳኔ ሂደቶች አልፈው ለጠቅላላ ጉባኤ ከቀረቡ በኋላ “ጠንካራ ተቃውሞ” የሚያጋጥማቸው አጀንዳዎች፤ ወደ ህዝበ ውሳኔ ”ሊመሩ” እንደሚችሉበሰነዱ ላይ ተጠቁሟል። በ30 ገጾች የተዘጋጀው ይህ ሰነድ...

“ኢትዮጵያ ውስጥ ኮሽ ሲል የሚነቁ፤ የጠላትነት ስሜት ያላቸው ሀገራት አሉ” – ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ...

“ኢትዮጵያ ውስጥ ኮሽ ሲል፤ ያደፈጡ፣ የሚነቁ፣ የዘመናት ያልተቋረጠ የጠላትነት ስሜት ያላቸው ሀገራት አሉ” ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ተናገሩ። ኢትዮጵያ “በቀጣይ” አዲስ ህገ መንግስት ሊኖራት እንደሚችልም ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጥቆማ ሰጥተዋል። አብይ ይህን ፍንጭ የሰጡት ዛሬ ረቡዕ ሐምሌ 8፤ 2018 ዓ.ም. በይፋ በተከፈተው የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ላይ ባደረጉት ንግግር ነው።...

“ሁሉም የዲጂታል ሚዲያዎች” ምዝገባ እንዲያከናውኑ ለማድረግ የሚያስችል የአዋጅ ማሻሻያ ሊደረግ ነው

በኢትዮጵያ የሚንቀሳቀሱ “ሁሉም የዲጂታል ሚዲያዎች” ወደ ምዝገባ ስርዓት እንዲገቡ ለማስቻል፤ በስራ ላይ ያለውን የመገናኛ ብዙሃን አዋጅ እስከ ማሻሻል የሚደርስ “የቅድመ ዝግጅት ሥራዎችን” እያከናወነ መሆኑን የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለስልጣን አስታወቀ። መስሪያ ቤቱ “በበየነ መረብ የሚያጋጥሙ” ባላቸው “የስነምግባር እና የህግ ጥሰቶች” ላይ “አስተዳደራዊ እርምጃ” እንደሚወስድም አስጠንቅቋል።  ባለስልጣኑ ይህን ያስታወቀው ትላንት ቅዳሜ ሐምሌ...

በአዲስ አበባ ከተማ ያሉ ሆቴሎች በመኝታ አገልግሎቶቻቸው ላይ አምስት በመቶ ተጨማሪ ታክስ ተጣለባቸው  

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ፤ የሆቴል እና መሰል አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ከሚሰጡት የመኝታ አገልግሎት ላይ አምስት በመቶ ታክስ እንዲሰበስቡ ግዴታ የሚጥል ደንብ ተግባራዊ አደረገ። ደንቡ ከትላንት በስቲያ ረቡዕ ሐምሌ 1፤ 2018 ጀምሮ ተግባራዊ መደረግ እንደሚጀምር ቢሮው ቢገልጽም፤ የሆቴል ባለቤቶች ግን ለመዘጋጃ የተሰጠው ጊዜ አጭር መሆኑን በመግለጽ ቅሬታቸውን አስምተዋል።...

“ህገ ወጥ የሲቪል ሰዎች ግድያ”፣ “ማሰቃየት” እና “ኢ-ሰብአዊ አያያዝ” በመጪዎቹ አምስት ዓመታት የሰብአዊ መብቶች...

“ህገ ወጥ የሲቪል ሰዎች ግድያ”፣ “የዘፈቀደ እና የተራዘመ እስር”፣ “አስገድዶ መሰወር እና ጠለፋ” እንዲሁም “ማሰቃየት እና ኢ-ሰብአዊ አያያዝ”፤ በቀጣዮቹ አምስት ዓመታት ለሰብአዊ መብቶች ትግበራ “ዋና ዋና ስጋቶች” እንደሚሆኑ የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ተነበየ። ኮሚሽኑ በነጻ ሚዲያ እና በጋዜጠኞች ላይ “እየጨመረ መጥቷል” ያለውን “ገደብ” እና በሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ላይ...

“በኢትዮጵያ ሉዓላዊነት ቅንጣት ታክል ስጋት የለም” – ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ

በትግራይ ክልል ዳግም ጦርነት እንዲቀሰቀስ “ሰፊ ፍላጎት” እንዳለ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ተናገሩ። በደርግ ዘመነ መንግስት “ሻዕቢያ እና ወያኔ፣ ከሱዳን ጋር ተባብረው” የወቅቱን አገዛዝ መጣላቸውን እና አሁንም ተመሳሳይ “ምኞት” እንዳለ የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ እነዚህ ወገኖች ብቻ ሳይሆኑ “ሌላም ቢጨመር በኢትዮጵያ ሉዓላዊነት ቅንጣት ታክል ስጋት የለም” ሲሉ ተደምጠዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ...

ገዢው ፓርቲ የስልጣን ገደብን ለሀገራዊ ምክክር በአጀንዳነት ማቅረቡን ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ አረጋገጡ 

ገዢው ብልጽግና ፓርቲ “በስልጣን ላይ ያለ መንግስት ለሁለት የስልጣን ዘመን ብቻ እንዲቆይ” ለሀገራዊ ምክክር ጉባኤ በአጀንዳነት ማቅረቡን ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ አረጋገጡ። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቀጣዩ የመንግስት ምስረታ ወቅት የበዓለ ሲመት ክብረ በዓል እንደማይኖርም ገልጸዋል። አብይ ይህን ያሉት፤ ዛሬ ማክሰኞ ሰኔ 30፤ 2018 በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ተገኝተው ከፓርላማ አባላት ለቀርቡላቸው ጥያቄዎች...

ዕድሜ ጠገቡ “ሲኒማ አምፒር” እና ሌሎች በቅርስ ተመዝግበው የነበሩ የፒያሳ ህንጻዎች ፈረሱ

በአዲስ አበባ ከተማ፣ ፒያሳ አካባቢ የሚገኙ እና ዕድሜያቸው ከ70 እስከ 100 ዓመት የሚጠጉ በቅርስነት የተመዘገቡ ህንጻዎች ፈረሱ። የፌደራል የቅርስ ጥናት እና ጥበቃ ባለስልጣን በበኩሉ “ሲኒማ አምፒርን” ጨምሮ የፈረሱት ህንጻዎች “የቅርስ መመዘኛ መስፈርቶችን የሚያሟሉ አይደሉም” ብሏል። በመዲናይቱ አራዳ ክፍለ ከተማ ከፈረሱ ህንጻዎች መካከል ሸዋ ሆቴል፣ በስተኋላ ላይ ወደ ሄርሞን ሆቴል የተለወጠው...

ተሰናባቾቹ የፓርላማ አባላት ላቀረቧቸው ጥያቄዎች ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ከነገ በስቲያ ምላሽ ሊሰጡ ነው...

ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ከነገ በስቲያ ማክሰኞ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በመገኘት፤ የ2018 በጀት ዓመት የስራ አፈጻጸም እና የቀጣዩን ዓመት በጀት አስመልክቶ ከተሰናባቾቹ የፓርላማ አባላት ለሚቀርቡላቸው ጥያቄዎች ማብራሪያ እንደሚሰጡ ምንጮች ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናገሩ። የፓርላማ አባላቱ ጥያቄዎቻቸውን እንዲያስገቡ ቀነ ገደብ የተሰጣቸው እስካለፈው ሰኞ እኩለ ቀን ድረስ እንደነበር ምንጮቹ ገልጸዋል። በ2008 ዓ.ም...

በትግራይ ክልል መቐለ ከተማ ውስጥ “የግዳጅ አፈሳ መጀመሩን” የዓይን እማኞች ተናገሩ

በትግራይ ክልል ዋና ከተማ መቐለ ከተማ የጸጥታ ኃይሎች “የወጣቶች አፈሳ” ማካሄድ መጀመራቸውን የዓይን እማኞች ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናገሩ። በመቐለ የቀድሞ ተዋጊዎች ወደ ምድቦቻቸው እንዲመለሱ ጥሪ ሲደረግ የነበረ ቢሆንም፤ ዛሬ የታዩ እንቅስቃሴዎች በተለያዩ የትግራይ አካባቢዎች ሲካሄድ የቆየው አፈሳ ወደ ክልሉ ዋና ከተማ በይፋ መድረሱን እንደሚጠቁም ጉዳዩን በቅርብ የሚከታተሉ የመረጃ ምንጮች አስረድተዋል። በከተማው...

አምስተኛውን ዙር የተራዘመ የብድር አቅርቦት ያጸደቀው አይ ኤም ኤፍ፤ 464 ሚሊዮን ዶላር ለኢትዮጵያ ለቀቀ 

የዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (አይ ኤፍ ኤም) የስራ አስፈጻሚ ቦርድ፤ ለኢትዮጵያ መንግስት 464 ሚሊዮን ዶላር ብድር “ወዲያውኑ እንዲለቀቅ” የሚያስችል ውሳኔ አሳለፈ። የድርጅቱ ስራ አስፈጻሚ ቦርድ ውሳኔውን ያሳለፈው፤ የኢትዮጵያን የተራዘመ ብድር አቅርቦት (ECF) አምስተኛ ዙር ግምግማን ከተመለከተ በኋላ ነው። የአይ ኤም ኤፍ ስራ አስፈጻሚ ቦርድ ለአራት ዓመታት የሚቆየውን የኢትዮጵያን የተራዘመ የብድር...