ዜና
በታገዱ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ላይ “ተጨማሪ ምርመራ” እየተከናወነ መሆኑን ተቆጣጣሪ ባለስልጣኑ አስታወቀ
በተስፋለም ወልደየስ
የእግድ እርምጃ በተወሰደባቸው የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ላይ ተጨማሪ “የማጣራት” እና “የምርመራ” ስራ እያከናወነ መሆኑን የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን አስታወቀ። ባለስልጣኑ በዚህ ምርምራ ግኝቱ ላይ ተመስርቶ፤ እግዱ “በመጨረሻ ማስጠንቀቂያ እንዲነሳ” ሊያደርግ አሊያም ድርጅቶቹ “እንዲፈርሱ” ወይም “እንዲሰረዙ” ለመስሪያ ቤቱ ቦርድ የውሳኔ ሃሳብ ሊያቀርብ እንደሚችልም ገልጿል።
የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች በተመዘገቡበት ዓላማ መሰረት...
ባለፉት ስድስት ወራት የተከሰተው የወባ ወረርሽኝ፤ አምና በተመሳሳይ ጊዜ ከነበረው “በሁለት እጥፍ” ጨምሯል ተባለ
በደምሰው ሺፈራው
የወባ ወረርሽኝ ስርጭት፤ ተፈናቃይ ዜጎች በሰፈሩባቸው አካባቢዎች እንዲሁም የመስኖ ስራ እና የስንዴ ልማት ባሉባቸው ቦታዎች ላይ “በእጅጉ መጨመሩን” የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ደረጀ ድጉማ ገለጹ። በኢትዮጵያ የተለያዩ አካባቢዎች ባለፈው ስድስት ወራት የተከሰተው የወባ ወረርሽኝ፤ ከአምናው ተመሳሳይ ጊዜ ጋር ሲነጻጸር “በሁለት እጥፍ” መጨመሩም ተነግሯል።
ይህ የተገለጸው ዛሬ ረቡዕ ጥር 28፤...
ከዩ.ኤስ.ኤይድ ገንዘብ የሚያገኙ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ንብረቶቻቸውን እንዳይሸጡ እና እንዳይስተላልፉ ክልከላ ተጣለባቸው
በደምሰው ሺፈራውየኢትዮጵያ ሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን፤ ከአሜሪካ ተራድኦ ድርጅት (USAID) የገንዘብ ድጋፍ የሚያገኙ ድርጅቶች ያለ መስሪያ ቤቱ “ግልጽ ፍቃድ”፤ ንብረት የማስተላለፍ፣ የማስወገድ እና የመሸጥ ድርጊቶችን እንዳያከናውኑ ከለከለ። መስሪያ ቤቱ የሰጠውን “ጥብቅ ማሳሰቢያ” በመተላለፍ በሚንቀሳቀሱ ድርጅቶች ላይ “ተገቢውን እርምጃ” እንደሚወስድም አስጠንቅቋል።
ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ማሳሰቢያውን እና ማስጠንቀቂያውን ያስተላለፈው፤ ዛሬ ማክሰኞ ጥር...
የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶችን አዋጅ እንዲያሻሽል፤ የፓርላማ ቋሚ ኮሚቴ ለተቆጣጣሪ መስሪያ ቤት አቅጣጫ ሰጠ
የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን የቦርድ ውክልናን ጨምሮ “በርካታ ክፍተቶች አሉበት” ያለውን የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች አዋጅ እንዲሻሻል ስራዎችን እያከናወነ መሆኑን ገለጸ። ባለስልጣኑ “አላሰራ ያሉ አዋጆችን እንዲሻሻሉ ለማድረግ” ለሚያከናወናቸው ስራዎች፤ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት “ተገቢውን ድጋፍ” እንደሚያደርግ ተገልጿል።
ይህ የተገለጸው የፓርላማው የህግና ፍትህ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ፤ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣንን የስራ እንቅስቃሴ...
መኢአድ ፓርቲውን በፕሬዝዳንት እና በምክትል ፕሬዝዳንትነት የሚመሩ አዲስ አመራሮችን መረጠ
በደምሰው ሽፈራው
የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ) ትላንት እሁድ ጥር 25፤ 2017 ባካሄደው ጠቅላላ ጉባኤ፤ የፓርቲው ተቀዳሚ ፕሬዝዳንት የነበሩትን አቶ አብርሃም ጌጡን ፓርቲውን እንዲመሩ መረጠ። ፓርቲው በዚሁ ጉባኤው፤ በመተዳደሪያ ደንቡ ላይ ማሻሻያ አድርጓል።
በኢትዮጵያ የምርጫ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባና የምርጫ ሥነምግባር አዋጅ መሰረት በምርጫ ቦርድ ተመዝግበው ህጋዊነት ያገኙ የፖለቲካ ፓርቲዎች፤ ቢያንስ በሶስት...
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በኢትዮጵያ ያሉ ግጭቶች ጠንሳሾች፤ “ትላንትና ፖለቲካ ሲያንቦራጭቁ የነበሩ ሰዎች ናቸው” አሉ
በኢትዮጵያ በተለያዩ አካባቢዎች ያሉ ግጭቶች “ጠንሳሽ” እና “ጨማቂዎች”፤ “ትላንትና ፖለቲካ ሲያንቦራጭቁ የነበሩ ሰዎች ናቸው” ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ወነጀሉ። አብይ በሚመሩት ብልጽግና ፓርቲ መደበኛ ጉባኤ መክፈቻ ላይ ዛሬ አርብ ባደረጉት ንግግር፤ ባለፉት ስድስት ዓመታት በኢትዮጵያ ውስጥ “ሰው torture አይደረግም” ሲሉ ተደምጠዋል።
ገዢው ፓርቲ እስከ መጪው እሁድ ጥር 25፤ 2017...
የኢህአዴግ ከፍተኛ አመራር የነበሩት አቶ ብርሃኑ አዴሎ፤ የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽንን እንዲመሩ ተሾሙ
በቤርሳቤህ ገብረ
በቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ የስልጣን ዘመን ለስድስት ዓመት ገደማ የካቤኔ ጉዳዮች ኃላፊ ሆነው የሰሩት አቶ ብርሃኑ አዴሎ፤ የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽንን (ኢሰመኮ) እንዲመሩ በፓርላማ ተሾሙ። አቶ ብርሃኑ የብሔራዊው የሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ኮሚሽነር የሆኑት፤ ተቋሙን ለአምስት ዓመታት የመሩትን ዶ/ር ዳንኤል በቀለን በመተካት ነው።
ዶ/ር ዳንኤል ከኃላፊነታቸው የተሰናበቱት፤ የስራ ዘመናቸው...
ኢዜማ ከመጪው ምርጫ ጋር “የተያያዘ በሚመስል መልኩ”፤ “አባላቶቼ እየታሰሩብኝ ነው” አለ
በደምሰው ሽፈራው
የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ ፓርቲ (ኢዜማ) 75 አባላቶቹ በእስር ላይ እንደሚገኙ አስታወቀ። ፓርቲው በአባሎቹ ላይ እስር እና ማዋከብ እየተፈጸመ የሚገኘው፤ ከአንድ ዓመት በኋላ ይካሄዳል ተብሎ ከሚጠበቀው ሀገራዊ ምርጫ ጋር “የተያያዘ በሚመስል መልኩ ነው” ሲል ወንጅሏል።
ኢዜማ ዛሬ ማክሰኞ ጥር 20፤ 2017 ባወጣው መግለጫ፤ በአባሎቹ ላይ ድርጊቶቹ እየተፈጸሙ ያሉት...
የግብርና ምርምር ተቋማት 312 ሄክታር መሬት “መነጠቃቸውን” የፓርላማ ቋሚ ኮሚቴ ይፋ አደረገ
የግብርና ምርምር እና የእንስሳት ብዜት ተቋማት “312 ሄክታር መሬት መነጠቃቸውን” በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የግብርና ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ይፋ አደረገ። መሬታቸውን ከተነጠቁ መካከል አንጋፋዎቹ የሆለታ፣ የጅማ እና የቢሾፍቱ የግብርና ምርምር ማዕከላት እንደሚገኙበት ቋሚ ኮሚቴው አስታውቋል።
ጉዳዩ የተነሳው የግብርና ሚኒስትሩ ዶ/ር ግርማ አመንቴ የመስሪያ ቤታቸውን የ2017 የመጀመሪያ መንፈቅ የስራ ሪፖርት፤ ትላንት...
ብልጽግና ፓርቲ በመጪው ጠቅላላ ጉባኤው የከፍተኛ አመራሮች ምርጫ ሊያካሄድ ነው
በደምሰው ሽፈራው
ከመጪው አርብ ጀምሮ ለተከታታይ ሶስት ቀናት በሚካሄደው የገዢው ፓርቲ ጠቅላላ ጉባኤ፤ ፓርቲውን የሚመሩ ከፍተኛ አመራሮች እንደሚመረጡ የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ አደም ፋራህ ተናገሩ። ለሁለተኛ ጊዜ በሚካሄደው በዚሁ ጠቅላላ ጉባኤ፤ የፓርቲው ፕሬዝዳንት፣ ምክትል ፕሬዝዳንቶችን ጨምሮ የስራ አስፈጻሚ እና የማዕከላዊ ኮሚቴ አባላት ምርጫ እንደሚካሄድ ምንጮች ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ገልጸዋል።
የብልጽግና ፓርቲ...
ለኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ካፒታል ማሳደጊያ የሚውል የ550 ሚሊዮን ዶላር ብድር በፓርላማ ጸደቀ
በቤርሳቤህ ገብረ
ለኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ካፒታል ማሳደጊያ የሚውል 550 ሚሊዮን ዶላርን ያካተተ የብድር ስምምነት፤ ዛሬ ሰኞ ጥር 19፤ 2017 በፓርላማ ጸደቀ። የካፒታል ማሳደጊያው፤ ባንኩን “የተሻለ ተወዳዳሪ” እና በቀጠናው መስራት የሚችል “ጠንካራ ባንክ እንዲሆን የሚያስችለው” ነው ተብሏል።
ለመንግስታዊው ባንክ ካፒታል ማሳደጊያ የሚውለው ገንዘብ፤ ዓለም አቀፉ የልማት ማህበር ለኢትዮጵያ መንግስት የሰጠው 700...
በጅማ ከተማ “በትንሹ 15 ሺህ ቤቶች መፍረሳቸውን” ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ተናገሩ
ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ከባለቤታቸው፣ ከሚኒስትሮች እና ከሌሎችም እንግዶች ጋር በመሆን፤ በኦሮሚያ ክልል ጅማ ከተማ እየተገነቡ ያሉ ፕሮጀክቶችን በትላንትናው ዕለት ተዘዋውረው ጉብኝተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከዚህ ጉብኝት በኋላ በሰጡት ገለጻ፤ በጅማ ከተማ ለተከናወኑ “የገበታ ለትውልድ” ፕሮጀክቶች “በትንሹ 15 ሺህ ቤቶች መፍረሳቸውን” ተናግረዋል።
በከተማይቱ የነበረ መስጂድ እና ከአንድ ሺህ በላይ የመቃብር ቦታ...
በሶማሊያ የሰላም ማስከበር ተልዕኮ የግብጽ ተሳትፎ፤ “የትኛውንም ሀገር የማስፈራራት ዓላማ” እንደሌለው የሀገሪቱ ፕሬዝዳንት ተናገሩ
የግብጽ በአዲሱ የአፍሪካ ህብረት የሶማሊያ ድጋፍ እና ማረጋጋት ተልዕኮ ውስጥ መሳተፍ “የትኛውንም ሀገር የማስፈራራት ዓላማ” እንደሌለው የሀገሪቱ ፕሬዝዳንት አብዱል ፋታህ አልሲሲ ተናገሩ። ፕሬዝዳንቱ “የሶማሊያን ደህንነት እና መረጋጋት ለማስፈን” ያለመ ባሉት አዲሱ ሰላም አስከባሪ ውስጥ፤ የግብጽ “ተሳትፎ አዎንታዊ” እንደሆነ ገልጸዋል።
አል ሲሲ በጉዳዩ ላይ አስተያየት የሰጡት ዛሬ ሐሙስ ጥር 15 ከሶማሊያ...
በማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ምክንያት የአምራች ኢንዱስትሪዎች የብር ፍላጎት “በእጥፍ መጨመሩን” የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ ተናገሩ
የኢትዮጵያ መንግስት ከስድስት ወራት በፊት ተግባራዊ ባደረገው የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ምክንያት፤ የሀገሪቱ የአምራች ኢንዱስትሪዎች “የብር ፍላጎት” “በእጥፍ እንደጨመረ” የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አለበል ተናገሩ። ሚኒስትሩ ባለፉት ስድስት ወራት ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የቀረበው ብድር “አጥጋቢ” እንዳልሆነ ዛሬ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አስረድተዋል።
አቶ መላኩ የመስሪያ ቤታቸውን የስራ አፈጻጸም ለፓርላማ ባቀረቡበት ወቅት...
የህዝብ ዕንባ ጠባቂ ተቋም አመራሮች ሹመት፤ የፓለቲካ ገለልተኝነትን “ጥያቄ ውስጥ ያስገባ ነው” የሚል ትችት...
በቤርሳቤህ ገብረ
የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ሹመታቸውን ያጸደቀላቸው የኢትዮጵያ የህዝብ ዕንባ ጠባቂ ተቋም አመራሮች የአመራረጥ ሂደት፤ “ከፓለቲካ ገለልተኝነት” ነጻ መሆን የሚለውን መስፈርት “ጥያቄ ውስጥ ያስገባ ነው” የሚል ትችት በፓርላማ አባል ቀረበበት። ተሿሚዎቹ ለፓርላማ የቀረቡት፤ የፖለቲካ ገለልተኝነትን ጨምሮ እያንዳንዱ ጉዳይ “በደንብ” እና “በዝርዝር” ታይቶ መሆኑን የተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ...