ምስላዊ መረጃ፦ ዛሬ የካቲት 22 ሊጀመር ቀን ተቆርጦለት የነበረውን የመራጮች ምዝገባ፤ ወደ ቀጣዩ ወር መጋቢት አጋማሽ መዛወሩን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አስታውቋል። ቦርዱ ለቀኑ መራዘም በምክንያትነት ከጠቀሳቸው ውስጥ የምርጫ ክልል ጽህፈት ቤቶችን ለመክፈት በክልል መንግስታት በኩል የታየው ዳተኝነት፣ የዕጩዎች ምዝገባ መራዘም እና የምርጫ ቁሳቁሶችን ለማጓጓዝ የገጠመው ተግዳሮት ይገኙባቸዋል። በተሻሻለው የጊዜ ሰሌዳ መሰረት የመራጮች ምዝገባ ከመጋቢት 16 ቀን ጀምሮ እስከ ሚያዝያ 15 ይካሄዳል ተብሏል። (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር)
አዳዲስ ዜና
ከ13 ወርቅ አምራች ኩባንያዎች በምርት ላይ የሚገኙት ሁለቱ ብቻ መሆናቸውን የማዕድን ሚኒስቴር አስታወቀ
በተስፋለም ወልደየስ
በኢትዮጵያ በከፍተኛ ወርቅ አምራችነት ከተመዘገቡ 13 ኩባንያዎች ውስጥ፤ በ2016 የመጀመሪያ ሩብ ዓመት ምርት ያመረቱት ሁለቱ ብቻ መሆናቸውን የማዕድን ሚኒስትሩ አቶ ሀብታሙ ተገኝ ተናገሩ። ቀሪዎቹ ኩባንያዎች በሚቀጥሉት ስድስት ወራት የስራ አፈጻጸማቸውን የማያስተካክሉ ከሆነ፤ የማዕድን...
የመከላከያ ሚኒስትሩ በክልሎች በየደረጃው ያሉ አመራሮች “አካባቢያቸውን ከሽፍቶች ማጽዳት አልቻሉም” ሲሉ ወቀሱ
በተስፋለም ወልደየስ
በክልሎች በተለያየ ደረጃ ያሉ የመንግስት አመራሮች “አካባቢያቸውን ከሽፍቶች ማጽዳት ባለመቻላቸው”፤ የመከላከያ ሰራዊት “የመንግስት መዋቅር ስራን ደርቦ እንዲሸፍን እየተገደደ ይገኛል” ሲሉ የመከላከያ ሚኒስትሩ ዶ/ር አብርሃም በላይ ወቀሱ። ሚኒስትሩ “የሽፍታ እንቅስቃሴ” ሲሉ የጠሩት ድርጊት እና በተለያዩ...
ኢትዮጵያ ወደብ ለማግኘት በምታደርገው ግፊት ወደ ጎረቤቶቿ “ጥይት የመተኮስ ፍላጎት” እንደሌላት ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ...
ኢትዮጵያ ወደብ ለማግኘት በምታደርገው ግፊት ወደ ሶማሊያ፣ ጅቡቲ፣ ኬንያ ወይም በሌሎች ጎረቤቶቿ ላይ “አንድ ጥይት የመተኮስ ፍላጎት” እንደሌላት ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ተናገሩ። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከተወካዮች ምክር ቤት አባላት ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች ዛሬ ማክሰኞ ህዳር 4፤...
ለምርጫ ቦርድ ሰብሳቢነት በዕጩነት የሚቀርቡ ሁለት ግለሰቦች ማንነት፤ እስከ ህዳር ወር ማብቂያ ባለው ጊዜ...
በተስፋለም ወልደየስ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢን የሚተኩ ዕጩዎችን እንዲመለምል የተቋቋመው ኮሚቴ፤ አጣርቶ የሚለያቸውን ሁለት ዕጩዎች የህዳር ወር ከመጠናቀቁ አስቀድሞ ለጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ እንደሚያቀርብ አስታወቀ። ኮሚቴው ጥቆማዎችን ከመጪው ሰኞ ህዳር 3፤ 2016 ጀምሮ ባሉት ተከታታይ...
አቶ ሳንዶካን ደበበ የጠቅላይ ሚኒስትር ልዩ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ሆነው ተሾሙ
በተስፋለም ወልደየስ
ላለፈው አንድ ዓመት በፕላን እና ልማት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ሆነው ሲሰሩ የቆዩት አቶ ሳንዶካን ደበበ፤ የጠቅላይ ሚኒስትር ልዩ ጽህፈት ቤት ኃላፊ (chief of staff) ሆነው ተሾሙ። ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ በሚኒስትር ዴኤታ ማዕረግ...