ምስላዊ መረጃ፦ ዛሬ የካቲት 22 ሊጀመር ቀን ተቆርጦለት የነበረውን የመራጮች ምዝገባ፤ ወደ ቀጣዩ ወር መጋቢት አጋማሽ መዛወሩን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አስታውቋል። ቦርዱ ለቀኑ መራዘም በምክንያትነት ከጠቀሳቸው ውስጥ የምርጫ ክልል ጽህፈት ቤቶችን ለመክፈት በክልል መንግስታት በኩል የታየው ዳተኝነት፣ የዕጩዎች ምዝገባ መራዘም እና የምርጫ ቁሳቁሶችን ለማጓጓዝ የገጠመው ተግዳሮት ይገኙባቸዋል። በተሻሻለው የጊዜ ሰሌዳ መሰረት የመራጮች ምዝገባ ከመጋቢት 16 ቀን ጀምሮ እስከ ሚያዝያ 15 ይካሄዳል ተብሏል። (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር)
Recent Posts
የሚኒስትሮች ምክር ቤት ዛሬ ጠዋት የተወያየበት የብድር ስምምነት ከሰዓት በፓርላማ ጸደቀ
የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ከሰዓት ባካሄደው ልዩ ስብሰባ፤ የዓለም ባንክ አካል ከሆነው ዓለም አቀፍ የልማት ማህበር የተገኘውን 600 ሚሊዮን ዶላር የብድር ስምምነት አጸደቀ። የብድር ስምምነቱን የያዘ የአዋጅ ሰነድ ለፓርላማ አባላት የተላከው፤ የሚኒስትሮች ምክር ቤት በጉዳዩ...
በትግራይ የሚደረጉ የሰላም ጥረቶችን “የሚያደናቅፉ” ላለቻቸው አካላት አሜሪካ ማሳሰቢያ ሰጠች
የአሜሪካ ኤምባሲ በትግራይ ክልል ያለውን ችግር ለመፍታት እየተካሄዱ ያሉ የሰላም ሂደቶችን “የሚያደናቅፉ” አካላት፤ በአፍሪካ ህብረት ለሚመራው የውይይት ጥረት “በአስቸኳይ ትብብር” እንዲያደርጉ አሳሰበ። የፖለቲካ መሪዎች የፕሪቶሪያ የግጭት ማቆም ስምምነትን “ሙሉ ለሙሉ” ተግባራዊ ማድረጋቸው “እጅግ አስፈላጊ” መሆኑንም...
ኢትዮጵያ የብሪክስ ልማት ባንክ አባል የምትሆንበት ረቂቅ አዋጅ ለተወካዮች ምክር ቤት ሊቀርብ ነው
የብሪክስ ሀገራት ያቋቋሙት የልማት ባንክን፤ ኢትዮጵያ በአባልነት እንድትቀላቀል የሚያስችላት የማጽደቂያ ረቂቅ አዋጅ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ተመራ። ረቂቅ አዋጁ በፓርላማ ጸድቆ ለባንኩ የገዢዎች ቦርድ ሲገባ፤ ኢትዮጵያ ከደቡብ አፍሪካ፣ ግብጽ እና አልጄሪያ በመቀጠል አራተኛዋ አፍሪካዊት የልማት...
እስከ አምስት ዓመት እስራት የሚያስቀጡ ጥፋቶች የተካተቱበት አዲሱ የመረጃ ነጻነት አዋጅ በፓርላማ ጸደቀ
ለ15 ዓመታት በስራ ላይ ከቆየው “የመገናኛ ብዙኃንና የመረጃ ነፃነት አዋጅ” የመገናኛ ብዙኃንን የሚመለከተው ክፍል ተለይቶ ሌላ ራሱን የቻለ ህግ እንዲወጣለት የተደረገው በ2013 ዓ.ም ነበር። የመረጃ ነጻነትን የሚመለከተው ቀሪው ክፍል በተመሳሳይ መልኩ አዋጅ ቢዘጋጅለትም፤ ለፓርላማ የሚቀርብበት...
የህገ መንግስት ማሻሻያ እና የመንግስት አደረጃጀት ጉዳይ በሀገራዊ የምክክር ጉባኤ ላይ በአጀንዳነት መያዛቸው ተገለጸ
ከመጪው ሐምሌ ወር መጀመሪያ ጀምሮ ለሶስት ሳምንት በሚካሄደው ሀገር አቀፍ የምክክር ጉባኤ ላይ ከሚቀርቡ አጀንዳዎች መካከል የህገ መንግስት ማሻሻያ እንዲሁም የመንግስት አደረጃጀት እና ቅርጽ እንደሚገኙበት ይፋ ተደረገ። የአዲስ አበባ እና የድሬዳዋ ከተሞች ጉዳይ እንዲሁም የምርጫ...

































