ምስላዊ መረጃ፦ ዛሬ የካቲት 22 ሊጀመር ቀን ተቆርጦለት የነበረውን የመራጮች ምዝገባ፤ ወደ ቀጣዩ ወር መጋቢት አጋማሽ መዛወሩን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አስታውቋል። ቦርዱ ለቀኑ መራዘም በምክንያትነት ከጠቀሳቸው ውስጥ የምርጫ ክልል ጽህፈት ቤቶችን ለመክፈት በክልል መንግስታት በኩል የታየው ዳተኝነት፣ የዕጩዎች ምዝገባ መራዘም እና የምርጫ ቁሳቁሶችን ለማጓጓዝ የገጠመው ተግዳሮት ይገኙባቸዋል። በተሻሻለው የጊዜ ሰሌዳ መሰረት የመራጮች ምዝገባ ከመጋቢት 16 ቀን ጀምሮ እስከ ሚያዝያ 15 ይካሄዳል ተብሏል። (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር)
Recent Posts
በኢትዮጵያ እና በግብጽ መካከል የሚካሄድን ድርድር ዳግም ለማስጀመር ዝግጁ መሆናቸውን ፕሬዝዳንት ትራምፕ ገለጹ
በግብጽ እና በኢትዮጵያ መካከል ያለውን የአባይን “ውሃ የመጋራት” ጥያቄ ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ “በኃላፊነት ለመፍታት”፤ የአሜሪካንን ሽምግልና ዳግም ለማስጀመር ዝግጁ መሆናቸውን የሀገሪቱ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ገለጹ። ፕሬዝዳንት ትራምፕ በታላቁ ህዳሴ ግድብ ዙሪያ ያለውን ውጥረት መፍታትን ቅድሚያ...
“ከእያንዳንዱ ግጭት ዕድል ማውጣት ነው የሚጠበቅብን” – ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ
ኢትዮጵያ ከሰሞኑ በተለያዩ የዓለም አካባቢዎች ያሉ “መናጦች” እና “መታወኮችን” ባትፈልግም፤ ከእያንዳንዱ ግጭት “ዕድል ፈልቅቃ ማውጣት” እንደሚጠበቅባት ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ተናገሩ። ዓለም ባልተናጠችበት ወቅት “ጥቅም አግኝተን፣ ስትናጥ እንደምንጎዳ ከእነሱ በላይ መጨነቅ የለብንም” ሲሉም ተደምጠዋል።
ጠቅላይ...
እነ አቶ ዮሃንስ ቧያለው የግል የስልክ ልውውጣቸው “ያለ ፍርድ ቤት ትዕዛዝ መጠለፉን” ለፍርድ ቤት...
የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባሉን አቶ ክርስቲያን ታደለን ጨምሮ በእነ ዮሃንስ ቧያለው መዝገብ ስር የሽብር ወንጀል ክስ የተመሰረተባቸው ተጠርጣሪዎች፤ በግል ስልካቸው ያደረጓቸው የድምጽ ልውውጦች “ያለ ፍርድ ቤት ትዕዛዝ መጠለፉን” ጉዳያቸውን ለሚመለከተው ችሎት አስታወቁ። ተከሳሾቹ በዐቃቤ...
የወልቃይት አካባቢ ህዝብ የፖለቲካ እጣ ፈንታውን “በራሱ እንዲወስን” እንዲደረግ የአሜሪካ አምባሳደር አሳሰቡ
የትግራይ እና የአማራ ክልሎች በሚወዛገቡበት የወልቃይት አካባቢ የሚኖረው ህዝብ፤ “በተገቢው ጊዜ” “የፖለቲካ እጣ ፈንታውን እንዲወስን” ሊደረግ እንደሚገባ በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ኧርቪን ማሲንጋ አሳሰቡ። የአካባቢዎች ነዋሪዎችን የወደፊት የኑሮ ሁኔታ በተመለከተ፤ አሜሪካ “በኢትዮጵያ የሚመራ” እና “በተባበሩት መንግስታት...
አዲስ አበባ 46ኛ የፍሳሽ ቆሻሻ ማጣሪያ ልታገኝ ነው
ለአዲስ አበባ ከተማ በአሁኑ ወቅት አገልግሎት እየሰጡ ከሚገኙ 45 የፍሳሽ ቆሻሻ ማጣሪያዎች ተጨማሪ የሆነ ጣቢያ ግንባታ ከትላንት በስቲያ መጀመሩን የከተማይቱ ውሃና ፍሳሽ ባለሥልጣን አስታወቀ። ጣቢያው በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ስር ያሉትን የካ፣ ቦሌ እና ለሚ...


































