ምስላዊ መረጃ፦ ዛሬ የካቲት 22 ሊጀመር ቀን ተቆርጦለት የነበረውን የመራጮች ምዝገባ፤ ወደ ቀጣዩ ወር መጋቢት አጋማሽ መዛወሩን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አስታውቋል። ቦርዱ ለቀኑ መራዘም በምክንያትነት ከጠቀሳቸው ውስጥ የምርጫ ክልል ጽህፈት ቤቶችን ለመክፈት በክልል መንግስታት በኩል የታየው ዳተኝነት፣ የዕጩዎች ምዝገባ መራዘም እና የምርጫ ቁሳቁሶችን ለማጓጓዝ የገጠመው ተግዳሮት ይገኙባቸዋል። በተሻሻለው የጊዜ ሰሌዳ መሰረት የመራጮች ምዝገባ ከመጋቢት 16 ቀን ጀምሮ እስከ ሚያዝያ 15 ይካሄዳል ተብሏል። (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር)
Recent Posts
ኢትዮ ቴሌኮም በ2019 በጀት ዓመት ገቢውን 295 ቢሊዮን ብር ለማድረስ ማቀዱን አስታወቀ
ኢትዮ ቴሌኮም በዘንድሮው በጀት ዓመት 295 ቢሊዮን ብር ገቢ ለማግኘት ማቀዱን አስታወቀ። ተቋሙ በ2019 በጀት ዓመት የደንበኞቹን ቁጥር ወደ 96.2 ሚሊዮን ለማድረስ እቅድ አለው።
መንግስታዊው የቴሌኮም አቅራቢ ኩባንያ ይህን የገለጸው፤ ለሶስት ዓመት ከያዘው ስትራቴጂ ውስጥ በዘንድሮው በጀት ዓመት...
የአሜሪካ የአፍሪካ ጉዳዮች ረዳት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ወደ ኢትዮጵያ ሊመጡ ነው
የአሜሪካ የአፍሪካ ጉዳዮች ረዳት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ፍራንክ ጋርሺያ ኢትዮጵያን ጨምሮ በሶስት የአፍሪካ ሀገራት ጉብኝት ሊያደርጉ ነው። ረዳት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ በኢትዮጵያ፣ ኬንያ እና ዛምቢያ የሚያደርጉት ጉብኝት፤ አሜሪካ ከየሀገራቱ ጋር ያላትን “ቁልፍ” የሁለትዮሽ ግንኙነቶች የማጠናከር...
ኢዜማ የሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ምክረ ሃሳቦችን የሚከታተል “ገለልተኛ እና ህጋዊ” አካል አንዲቋቋም ጠየቀ
የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትህ ፓርቲ (ኢዜማ) ሀገር አቀፍ የምክክር ጉባኤ ላይ የቀረቡ ምክረ ሃሳቦችን አተገባበር የሚከታተል “ገለልተኛ እና ሕጋዊ” አካል አንዲቋቋም ጥያቄ አቀረበ። የፌደራል መንግስት ምክረ ሃሳቦቹን ለመተግበር “ከተገቢው በላይ ጊዜ እንዳይወስድ” እና አፈጻጸሙን “በፍጥነት”...
ከዘንድሮ የ12ኛ ክፍል ተፈታኞች መካከል 87.2 በመቶው ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚያሳልፍ ውጤት ማምጣት አልቻሉም
በዘንድሮው የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ መልቀቂያ ፈተና በተመዘገበው ውጤት “በአብዛኛው ደስተኞች ነን” ሲሉ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ተናገሩ። ሚኒስትሩ ይህን ያሉት ከተፈታኝ ተማሪዎች መካከል 87.2 በመቶው ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚያሳልፋቸው ውጤት ማምጣት ሳይችሉ በቀሩበት እና...
በአዲስ አበባ ከተማ ጉዳይ አቀራራቢ ሃሳቦችን እንዲያዘጋጅ የተቋቋመው ኮሚቴ፤ አስማሚ ምክረ ሃሳቦችን ዛሬ ያቀርባል...
በሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ላይ ውዝግብ እና አለመግባባት በፈጠረው የአዲስ አበባ ከተማ ጉዳይ ላይ አስማሚ ሃሳብ እንዲያዘጋጅ የተቋቋመው አቀራራቢ ኮሚቴ፤ የደረሰበትን ውጤት በዛሬው ዕለት ለተመካካሪዎች እንዲያቀርብ መወሰኑን የጉባኤው ተሳታፊዎች ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ገለጹ። ኮሚቴው አስማሚ ሃሳቡን የሚያዘጋጀው፤...


































