ምስላዊ መረጃ፦ ዛሬ የካቲት 22 ሊጀመር ቀን ተቆርጦለት የነበረውን የመራጮች ምዝገባ፤ ወደ ቀጣዩ ወር መጋቢት አጋማሽ መዛወሩን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አስታውቋል። ቦርዱ ለቀኑ መራዘም በምክንያትነት ከጠቀሳቸው ውስጥ የምርጫ ክልል ጽህፈት ቤቶችን ለመክፈት በክልል መንግስታት በኩል የታየው ዳተኝነት፣ የዕጩዎች ምዝገባ መራዘም እና የምርጫ ቁሳቁሶችን ለማጓጓዝ የገጠመው ተግዳሮት ይገኙባቸዋል። በተሻሻለው የጊዜ ሰሌዳ መሰረት የመራጮች ምዝገባ ከመጋቢት 16 ቀን ጀምሮ እስከ ሚያዝያ 15 ይካሄዳል ተብሏል። (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር)
Recent Posts
“ኢትዮጵያ ውስጥ ኮሽ ሲል የሚነቁ፤ የጠላትነት ስሜት ያላቸው ሀገራት አሉ” – ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ...
“ኢትዮጵያ ውስጥ ኮሽ ሲል፤ ያደፈጡ፣ የሚነቁ፣ የዘመናት ያልተቋረጠ የጠላትነት ስሜት ያላቸው ሀገራት አሉ” ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ተናገሩ። ኢትዮጵያ “በቀጣይ” አዲስ ህገ መንግስት ሊኖራት እንደሚችልም ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጥቆማ ሰጥተዋል።
አብይ ይህን ፍንጭ የሰጡት ዛሬ ረቡዕ...
“ሁሉም የዲጂታል ሚዲያዎች” ምዝገባ እንዲያከናውኑ ለማድረግ የሚያስችል የአዋጅ ማሻሻያ ሊደረግ ነው
በኢትዮጵያ የሚንቀሳቀሱ “ሁሉም የዲጂታል ሚዲያዎች” ወደ ምዝገባ ስርዓት እንዲገቡ ለማስቻል፤ በስራ ላይ ያለውን የመገናኛ ብዙሃን አዋጅ እስከ ማሻሻል የሚደርስ “የቅድመ ዝግጅት ሥራዎችን” እያከናወነ መሆኑን የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለስልጣን አስታወቀ። መስሪያ ቤቱ “በበየነ መረብ የሚያጋጥሙ” ባላቸው...
በአዲስ አበባ ከተማ ያሉ ሆቴሎች በመኝታ አገልግሎቶቻቸው ላይ አምስት በመቶ ተጨማሪ ታክስ ተጣለባቸው
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ፤ የሆቴል እና መሰል አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ከሚሰጡት የመኝታ አገልግሎት ላይ አምስት በመቶ ታክስ እንዲሰበስቡ ግዴታ የሚጥል ደንብ ተግባራዊ አደረገ። ደንቡ ከትላንት በስቲያ ረቡዕ ሐምሌ 1፤ 2018 ጀምሮ ተግባራዊ መደረግ...
“ህገ ወጥ የሲቪል ሰዎች ግድያ”፣ “ማሰቃየት” እና “ኢ-ሰብአዊ አያያዝ” በመጪዎቹ አምስት ዓመታት የሰብአዊ መብቶች...
“ህገ ወጥ የሲቪል ሰዎች ግድያ”፣ “የዘፈቀደ እና የተራዘመ እስር”፣ “አስገድዶ መሰወር እና ጠለፋ” እንዲሁም “ማሰቃየት እና ኢ-ሰብአዊ አያያዝ”፤ በቀጣዮቹ አምስት ዓመታት ለሰብአዊ መብቶች ትግበራ “ዋና ዋና ስጋቶች” እንደሚሆኑ የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ተነበየ። ኮሚሽኑ...
“በኢትዮጵያ ሉዓላዊነት ቅንጣት ታክል ስጋት የለም” – ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ
በትግራይ ክልል ዳግም ጦርነት እንዲቀሰቀስ “ሰፊ ፍላጎት” እንዳለ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ተናገሩ። በደርግ ዘመነ መንግስት “ሻዕቢያ እና ወያኔ፣ ከሱዳን ጋር ተባብረው” የወቅቱን አገዛዝ መጣላቸውን እና አሁንም ተመሳሳይ “ምኞት” እንዳለ የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ እነዚህ ወገኖች...

































