ዜና

“ኢትዮጵያ ውስጥ ኮሽ ሲል የሚነቁ፤ የጠላትነት ስሜት ያላቸው ሀገራት አሉ” – ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ

“ኢትዮጵያ ውስጥ ኮሽ ሲል፤ ያደፈጡ፣ የሚነቁ፣ የዘመናት ያልተቋረጠ የጠላትነት ስሜት ያላቸው ሀገራት አሉ” ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ተናገሩ። ኢትዮጵያ “በቀጣይ” አዲስ ህገ መንግስት ሊኖራት እንደሚችልም ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጥቆማ ሰጥተዋል። አብይ ይህን ፍንጭ የሰጡት ዛሬ ረቡዕ ሐምሌ 8፤ 2018 ዓ.ም. በይፋ በተከፈተው የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ላይ ባደረጉት ንግግር ነው። በአዲስ አበባ በሚገኘው በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል በተካሄደው በዚሁ...

“ሁሉም የዲጂታል ሚዲያዎች” ምዝገባ እንዲያከናውኑ ለማድረግ የሚያስችል የአዋጅ ማሻሻያ ሊደረግ ነው

በኢትዮጵያ የሚንቀሳቀሱ “ሁሉም የዲጂታል ሚዲያዎች” ወደ ምዝገባ ስርዓት እንዲገቡ ለማስቻል፤ በስራ ላይ ያለውን የመገናኛ ብዙሃን አዋጅ እስከ ማሻሻል የሚደርስ “የቅድመ ዝግጅት ሥራዎችን” እያከናወነ መሆኑን...

በአዲስ አበባ ከተማ ያሉ ሆቴሎች በመኝታ አገልግሎቶቻቸው ላይ አምስት በመቶ ተጨማሪ ታክስ ተጣለባቸው  

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ፤ የሆቴል እና መሰል አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ከሚሰጡት የመኝታ አገልግሎት ላይ አምስት በመቶ ታክስ እንዲሰበስቡ ግዴታ የሚጥል ደንብ ተግባራዊ...

“ህገ ወጥ የሲቪል ሰዎች ግድያ”፣ “ማሰቃየት” እና “ኢ-ሰብአዊ አያያዝ” በመጪዎቹ አምስት ዓመታት የሰብአዊ መብቶች...

“ህገ ወጥ የሲቪል ሰዎች ግድያ”፣ “የዘፈቀደ እና የተራዘመ እስር”፣ “አስገድዶ መሰወር እና ጠለፋ” እንዲሁም “ማሰቃየት እና ኢ-ሰብአዊ አያያዝ”፤ በቀጣዮቹ አምስት ዓመታት ለሰብአዊ መብቶች ትግበራ “ዋና ዋና ስጋቶች” እንደሚሆኑ የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ተነበየ። ኮሚሽኑ በነጻ ሚዲያ እና በጋዜጠኞች ላይ “እየጨመረ መጥቷል” ያለውን “ገደብ” እና በሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ላይ...

“በኢትዮጵያ ሉዓላዊነት ቅንጣት ታክል ስጋት የለም” – ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ

በትግራይ ክልል ዳግም ጦርነት እንዲቀሰቀስ “ሰፊ ፍላጎት” እንዳለ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ተናገሩ። በደርግ ዘመነ መንግስት “ሻዕቢያ እና ወያኔ፣ ከሱዳን ጋር ተባብረው” የወቅቱን አገዛዝ መጣላቸውን እና አሁንም ተመሳሳይ “ምኞት” እንዳለ የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ እነዚህ ወገኖች ብቻ ሳይሆኑ “ሌላም ቢጨመር በኢትዮጵያ ሉዓላዊነት ቅንጣት ታክል ስጋት የለም” ሲሉ ተደምጠዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ...

ገዢው ፓርቲ የስልጣን ገደብን ለሀገራዊ ምክክር በአጀንዳነት ማቅረቡን ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ አረጋገጡ 

ገዢው ብልጽግና ፓርቲ “በስልጣን ላይ ያለ መንግስት ለሁለት የስልጣን ዘመን ብቻ እንዲቆይ” ለሀገራዊ ምክክር ጉባኤ በአጀንዳነት ማቅረቡን ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ አረጋገጡ። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቀጣዩ የመንግስት ምስረታ ወቅት የበዓለ ሲመት ክብረ በዓል እንደማይኖርም ገልጸዋል። አብይ ይህን ያሉት፤ ዛሬ ማክሰኞ ሰኔ 30፤ 2018 በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ተገኝተው ከፓርላማ አባላት ለቀርቡላቸው ጥያቄዎች...

ዕድሜ ጠገቡ “ሲኒማ አምፒር” እና ሌሎች በቅርስ ተመዝግበው የነበሩ የፒያሳ ህንጻዎች ፈረሱ

በአዲስ አበባ ከተማ፣ ፒያሳ አካባቢ የሚገኙ እና ዕድሜያቸው ከ70 እስከ 100 ዓመት የሚጠጉ በቅርስነት የተመዘገቡ ህንጻዎች ፈረሱ። የፌደራል የቅርስ ጥናት እና ጥበቃ ባለስልጣን በበኩሉ “ሲኒማ አምፒርን” ጨምሮ የፈረሱት ህንጻዎች “የቅርስ መመዘኛ መስፈርቶችን የሚያሟሉ አይደሉም” ብሏል። በመዲናይቱ አራዳ ክፍለ ከተማ ከፈረሱ ህንጻዎች መካከል ሸዋ ሆቴል፣ በስተኋላ ላይ ወደ ሄርሞን ሆቴል የተለወጠው...

ተሰናባቾቹ የፓርላማ አባላት ላቀረቧቸው ጥያቄዎች ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ከነገ በስቲያ ምላሽ ሊሰጡ ነው...

ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ከነገ በስቲያ ማክሰኞ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በመገኘት፤ የ2018 በጀት ዓመት የስራ አፈጻጸም እና የቀጣዩን ዓመት በጀት አስመልክቶ ከተሰናባቾቹ የፓርላማ አባላት ለሚቀርቡላቸው ጥያቄዎች ማብራሪያ እንደሚሰጡ ምንጮች ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናገሩ። የፓርላማ አባላቱ ጥያቄዎቻቸውን እንዲያስገቡ ቀነ ገደብ የተሰጣቸው እስካለፈው ሰኞ እኩለ ቀን ድረስ እንደነበር ምንጮቹ ገልጸዋል። በ2008 ዓ.ም...

በትግራይ ክልል መቐለ ከተማ ውስጥ “የግዳጅ አፈሳ መጀመሩን” የዓይን እማኞች ተናገሩ

በትግራይ ክልል ዋና ከተማ መቐለ ከተማ የጸጥታ ኃይሎች “የወጣቶች አፈሳ” ማካሄድ መጀመራቸውን የዓይን እማኞች ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናገሩ። በመቐለ የቀድሞ ተዋጊዎች ወደ ምድቦቻቸው እንዲመለሱ ጥሪ ሲደረግ የነበረ ቢሆንም፤ ዛሬ የታዩ እንቅስቃሴዎች በተለያዩ የትግራይ አካባቢዎች ሲካሄድ የቆየው አፈሳ ወደ ክልሉ ዋና ከተማ በይፋ መድረሱን እንደሚጠቁም ጉዳዩን በቅርብ የሚከታተሉ የመረጃ ምንጮች አስረድተዋል። በከተማው...

አምስተኛውን ዙር የተራዘመ የብድር አቅርቦት ያጸደቀው አይ ኤም ኤፍ፤ 464 ሚሊዮን ዶላር ለኢትዮጵያ ለቀቀ 

የዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (አይ ኤፍ ኤም) የስራ አስፈጻሚ ቦርድ፤ ለኢትዮጵያ መንግስት 464 ሚሊዮን ዶላር ብድር “ወዲያውኑ እንዲለቀቅ” የሚያስችል ውሳኔ አሳለፈ። የድርጅቱ ስራ አስፈጻሚ ቦርድ ውሳኔውን ያሳለፈው፤ የኢትዮጵያን የተራዘመ ብድር አቅርቦት (ECF) አምስተኛ ዙር ግምግማን ከተመለከተ በኋላ ነው። የአይ ኤም ኤፍ ስራ አስፈጻሚ ቦርድ ለአራት ዓመታት የሚቆየውን የኢትዮጵያን የተራዘመ የብድር...

ህወሓት ከፌደራል መንግስት ሊደራደር የሚችለው “በሶስተኛ ሀገር” እንደሆነ የፓርቲው ጽህፈት ቤት ኃላፊ ጥቆማ ሰጡ

ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) ከፌደራል መንግስት ጋር የሚደራደር ከሆነ በአዲስ አበባ ከተማ ሳይሆን “በሌላ ሶስተኛ ሀገር” እንደሚሆን ለአሜሪካ ማሳወቁን የፓርቲው ጽህፈት ቤት ኃላፊ ፈትለወርቅ ገብረእግዚአብሔር ተናገሩ። የአሜሪካ መንግስት “ቪዛ መከልከል ይቅር እና ሌላ ቢያደርግም”፤ “የትግራይ ህዝብ ህልውናን ለማረጋገጥ” ህወሓት “እስከ መጨረሻ እንደሚታገል” ኃላፊዋ ገልጸዋል።  “ሞንጆሪኖ” በሚለው የቅጽል ስማቸው ይበልጡኑ...

የአውሮፓ ህብረት የህወሓት “የተናጠል የግዳጅ ወታደራዊ ምልመላ”፤ የፕሪቶሪያ ስምምነት ድንጋጌዎችን “የጣሰ ነው” አለ  

ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) የትግራይ ክልል ምክር ቤትን ወደ ስራ መመለሱ እና “የተናጠል የግዳጅ ወታደራዊ ምልመላን” ተግባራዊ ማድረጉ፤ “የፕሪቶሪያ ስምምነት ድንጋጌዎችን የሚጥስ ነው” ሲል በኢትዮጵያ የአውሮፓ ህብረት ልዑክ ተቸ። የፕሪቶሪያ ስምምነትን በተጨባጭ ተፈጻሚ ለማድረግ፤ በሁሉም ወገኖች የሚደረጉ ውይይቶች “በአስቸኳይ” በድጋሚ መጀመር እንዳለባቸውም ልዑኩ አሳስቧል።  የአውሮፓ ህብረት ልዑክ ይህን ያለው፤...

የሚኒስትሮች ምክር ቤት ዛሬ ጠዋት የተወያየበት የብድር ስምምነት ከሰዓት በፓርላማ ጸደቀ 

የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ከሰዓት ባካሄደው ልዩ ስብሰባ፤ የዓለም ባንክ አካል ከሆነው ዓለም አቀፍ የልማት ማህበር የተገኘውን 600 ሚሊዮን ዶላር የብድር ስምምነት አጸደቀ። የብድር ስምምነቱን የያዘ የአዋጅ ሰነድ ለፓርላማ አባላት የተላከው፤ የሚኒስትሮች ምክር ቤት በጉዳዩ ላይ ተወያይቶ ውሳኔ ከማሳለፉ አስቀድሞ ነው።  የሚኒስትሮች ምክር ቤት ከዓለም አቀፍ የልማት ማህበር ጋር የፊርማ...

በትግራይ የሚደረጉ የሰላም ጥረቶችን “የሚያደናቅፉ” ላለቻቸው አካላት አሜሪካ ማሳሰቢያ ሰጠች   

የአሜሪካ ኤምባሲ በትግራይ ክልል ያለውን ችግር ለመፍታት እየተካሄዱ ያሉ የሰላም ሂደቶችን “የሚያደናቅፉ” አካላት፤ በአፍሪካ ህብረት ለሚመራው የውይይት ጥረት “በአስቸኳይ ትብብር” እንዲያደርጉ አሳሰበ። የፖለቲካ መሪዎች የፕሪቶሪያ የግጭት ማቆም ስምምነትን “ሙሉ ለሙሉ” ተግባራዊ ማድረጋቸው “እጅግ አስፈላጊ” መሆኑንም ኤምባሲው ገልጿል። ኤምባሲው ይህን የገለጸው፤ በትግራይ ክልል ያለውን ሁኔታ በተመለከተ በቃል አቃባዩ በኩል ዛሬ አርብ...

ኢትዮጵያ የብሪክስ ልማት ባንክ አባል የምትሆንበት ረቂቅ አዋጅ ለተወካዮች ምክር ቤት ሊቀርብ ነው

የብሪክስ ሀገራት ያቋቋሙት የልማት ባንክን፤ ኢትዮጵያ በአባልነት እንድትቀላቀል የሚያስችላት የማጽደቂያ ረቂቅ አዋጅ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ተመራ። ረቂቅ አዋጁ በፓርላማ ጸድቆ ለባንኩ የገዢዎች ቦርድ ሲገባ፤ ኢትዮጵያ ከደቡብ አፍሪካ፣ ግብጽ እና አልጄሪያ በመቀጠል አራተኛዋ አፍሪካዊት የልማት ባንኩ አባል አገር ትሆናለች።   ዋና መስሪያ ቤቱን በቻይና ሻንጋይ ከተማ ያደረገው የብሪክስ የልማት ባንክ፤...

እስከ አምስት ዓመት እስራት የሚያስቀጡ ጥፋቶች የተካተቱበት አዲሱ የመረጃ ነጻነት አዋጅ በፓርላማ ጸደቀ 

ለ15 ዓመታት በስራ ላይ ከቆየው “የመገናኛ ብዙኃንና የመረጃ ነፃነት አዋጅ” የመገናኛ ብዙኃንን የሚመለከተው ክፍል ተለይቶ ሌላ ራሱን የቻለ ህግ እንዲወጣለት የተደረገው በ2013 ዓ.ም ነበር። የመረጃ ነጻነትን የሚመለከተው ቀሪው ክፍል በተመሳሳይ መልኩ አዋጅ ቢዘጋጅለትም፤ ለፓርላማ የሚቀርብበት ሂደት ተጓትቶ ቆይቷል።  ከዓመታት ጥበቃ በኋላ የመረጃ ነጻነትን ለመደንገግ የተዘጋጀው የአዋጅ ረቂቅ፤ ከሁለት ወራት በፊት...

የህገ መንግስት ማሻሻያ እና የመንግስት አደረጃጀት ጉዳይ በሀገራዊ የምክክር ጉባኤ ላይ በአጀንዳነት መያዛቸው ተገለጸ

ከመጪው ሐምሌ ወር መጀመሪያ ጀምሮ ለሶስት ሳምንት በሚካሄደው ሀገር አቀፍ የምክክር ጉባኤ ላይ ከሚቀርቡ አጀንዳዎች መካከል የህገ መንግስት ማሻሻያ እንዲሁም የመንግስት አደረጃጀት እና ቅርጽ እንደሚገኙበት ይፋ ተደረገ። የአዲስ አበባ እና የድሬዳዋ ከተሞች ጉዳይ እንዲሁም የምርጫ ስርዓት በሀገር አቀፍ ጉባኤው ለምክክር ከሚቀርቡት አጀንዳዎች ውስጥ ተካትተዋል። የምክክር አጀንዳዎቹን ዛሬ ረቡዕ ሰኔ 17፤...

የትግራይ ክልል ባለስልጣናት ስራ ላይ ያዋሉትን “ጨቋኝ ሕግ” እንዲሽሩ ሂውማን ራይትስ ዎች ጥሪ አቀረበ

ዓለም አቀፉ የሰብአዊ መብቶች ተሟጋች ድርጅት ሂውማን ራይትስ ዎች “የግዳጅ ወታደራዊ ምልመላ” ለማካሄድ እና “ተቃውሞን ለመቅጣት ስልጣን ይሰጣል”  ያለውን በትግራይ ክልል ስራ ላይ የዋለ ህግ እንዲሻር ለክልሉ ባለስልጣናት ጥሪ አቀረበ። የትግራይ ክልል ምክር ቤት ባለፈው ግንቦት ወር መጨረሻ ስራ ላይ ያዋለው ህግ፤ “ኤርትራ ከምትከተለው አስገዳጅ የብሔራዊ አገልግሎት ጋር ምስስሎሽ...