ዜና
የ12ኛ ክፍል ፈተናን ሙሉ ለመሉ በበይነ መረብ ለመስጠት መታቀዱ፤ የፍትሃዊነት እና የተፈጻሚነት ጥያቄ በፓርላማ...
ዘንድሮ የ12ተኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተናን ሙሉ ለሙሉ በበይነ መረብ ለመስጠት መታቀዱ፤ የመሰረተ ልማት ባልተሟላባቸው አካባቢዎች ባሉ ተማሪዎች ውጤት ላይ “ከፍተኛ አሉታዊ ተጽዕኖ” ሊኖረው እንደሚችል የፓርላማ አባላት ስጋታቸውን ገለጹ። ትምህርት ሚኒስቴር በበኩሉ 122 ሺህ የመፈተኛ ኮምፒውተሮች መዘጋጀታቸውን እና ጉዳዩን በቅርበት የሚከታተል የተለያዩ የመንግስት አካላትን የያዘ ግብረ ኃይል መቋቋሙን ገልጿል።
ይህ...
ኢትዮጵያ በስምንት ወራት ውስጥ ከወጪ ንግድ 6.76 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ማግኘቷ ተገለጸ
ኢትዮጵያ በዘንድሮው በጀት ዓመት ስምንት ወራት ከወጪ ንግድ 6.76 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ማግኘቷን የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር አስታወቀ። ይህ የገንዘብ መጠን ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር ከ2.4 ቢሊዮን ዶላር በላይ እድገት ያለው መሆኑንም ሚኒስቴሩ ገልጿል።
ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ይህን የገለጸው፤ ዛሬ ረቡዕ መጋቢት 23፤ 2018 የስምንት ወራት የስራ አፈጻጸም...
በጋምቤላ ክልል የጸጥታ መደፍረስ “ተሳትፎ ነበራቸው” የተባሉ 62 የፖሊስ አባላት ጉዳይ በህግ እየታየ መሆኑ...
በጋምቤላ ክልል ተከስቶ በነበረው የጸጥታ መደፍረስ ወቅት “በጥፋት ድርጊቶች ውስጥ ተሳታፊ መሆናቸው ተረጋግጧል” ከተባሉ 272 የፖሊስ አባላት ውስጥ የ62ቱ ጉዳይ በህግ እየታየ መሆኑን አንድ የክልሉ ከፍተኛ ኃላፊ ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናገሩ። ከዚህ ክስተት ጋር በተያያዘ በአጠቃላይ 642 የፖሊስ እና የአድማ ብተና አባላትን ከስራ ማሰናበቱን የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን አስታውቋል።
ኮሚሽኑ በክልሉ ፖሊሶች...
የትግራይ ክልል አጀንዳ ማሰባሰብ በመጪው ሳምንት በአዲስ አበባ ሊካሄድ ነው
ከትግራይ ክልል ለሀገራዊ ምክክር የሚቀርቡ አጀንዳዎች የሚሰበሰቡበት መርሃ ግብር በመጪው ሳምንት በአዲስ አበባ ከተማ እንደሚካሄድ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን አስታወቀ። በመርሃ ግብሩ የትግራይ ክልል ተወላጅ የሆኑ ላይ 400 ተሳታፊዎች ይገኛሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ ኮሚሽኑ ገልጿል።
ከተሳታፊዎቹ ውስጥ ምሁራን፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች እና የሲቪክ ማህበረሰብ ድርጅቶች ተወካዮች እንደሚገኙበት የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር...
የሽብር ወንጀል ተከሳሿ ጋዜጠኛ ገነት አስማማው፤ ከጋጠማት የጤና እክል ጋር በተያያዘ ለፍርድ ቤት አቤቱታ አቀረበች
በሽብር ወንጀል ተጠርጥራ ሶስት ዓመት ለሚጠጋ ጊዜ በእስር ላይ ያለችው ጋዜጠኛ ገነት አስማማው፤ ባጋጠማት የጤና እክል ምክንያት በራሷ ወጪ ፍራሽ ለመግዛት እንዲፈቀድላት ለፍርድ ቤት ጥያቄ አቀረበች። ጋዜጠኛዋ ጥያቄዋን በዛሬው ዕለት በጠበቃዋ በኩል ያቀረበችው ለፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ነው።
የተከሳሿ ጠበቃ አቶ ሰለሞን ገዛኸኝ ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” እንደተናገሩት፤ ጋዜጠኛ ገነት ባለፉት ሁለት ዓመታት በኩላሊት ህመም...
ፓርላማው “ምልዓተ ጉባኤ ማሟላት” ባለመቻሉ መደበኛ ስብሰባውን ሳያካሄድ ቀረ
የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በዛሬው ዕለት ሊያካሄደው የነበረውን መደበኛ ስብሰባ፤ የፓርላማ አባላት ምልዓተ ጉባኤ ሳይሟላ በመቅረቱ ለመሰረዝ ተገደደ። ምክር ቤቱ ውሳኔውን ከማስተላለፉ አስቀድሞ፤ የፓርላማው ሰራተኞች “ዝግ ስብሰባ” እንደሚደረግ በመግለጽ ጋዜጠኞች ከስብሰባ አዳራሽ እንዲወጡ አድርገዋል።
መደበኛ ስብሰባዎቹን ዘወትር ማክሰኞ እና ሐሙስ የሚያካሄደው የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት፤ ለዛሬ መጋቢት 10፤ 2018 በስድስት...
በኢትዮጵያ እና ኬንያ የኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ ፕሮጀክት “በመመሳጠር” እና “ማጭበርበር” ተሳትፈዋል የተባሉ ኩባንያዎች እገዳ...
ከኢትዮጵያ ወደ ኬንያ የተዘረጋው የኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ የመጀመሪያ ምዕራፍ አማካሪ እና ሁለት እህት ኩባንያዎቹ፤ በዓለም ባንክ የገንዘብ ድጋፍ በሚከናወኑ ስራዎች ለ21 ወራት እንዳይሳተፉ ታገዱ። ኩባንያዎቹ የታገዱት “በምስራቅ አፍሪካ የኤሌክትሪክ ሀይዌይ ፕሮጀክት” ውስጥ ፈጽመዋቸዋል በተባሉ “የመመሳጠር” እና “የማጭበርበር” ድርጊቶች ምክንያት ነው።
የምስራቅ አፍሪካ የኤሌክትሪክ ሀይዌይ ፕሮጀክት፤ ከወላይታ ሶዶ እስከ ኬንያዋ ሱስዋ...
ከሚቀጥለው ሳምንት ጀምሮ ለአሜሪካ ቪዛ የሚያመለክቱ ኢትዮጵያውያን 2.3 ሚሊዮን ብር ገደማ ዋስትና የማስያዝ ግዴታ...
ለንግድ ስራዎች እና ለቱሪዝም ወደ አሜሪካ የሚገቡ ዜጎቻቸው 15 ሺህ ዶላር ዋስትና እንዲያስዙ ከሚገደዱ ሀገራት መካከል ኢትዮጵያ ተካተተች። ዋስትና የማስያዝ አሰራሩ ከኢትዮጵያውያን በተጨማሪ በ11 ሀገራት ዜጎች ላይ ከመጪው ሳምንት ጀምሮ ተፈጻሚ እንደሚሆን የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት አስታውቋል።
የአሜሪካ መንግስት “ከተፈቀደላቸው ጊዜ በላይ በህገ ወጥ መንገድ በሀገሩ የሚቆዩ ሰዎችን ለመከላከል”...
የትምህርት ተቋማት ድንጋጌዎችን ተላልፈው ሲገኙ፤ ከወርሃዊ ገቢያቸው 35 በመቶውን “ለመንግስት ገቢ እንዲያደርጉ” የሚያስገድድ ደንብ...
አግባብነት ባለው አካል “ተገምግሞ ፈቃድ ያልተሰጠው” መጽሐፍ “ለተማሪዎች ሲሸጡ” ወይም “ሲጠቀሙ” የተገኙ በአዲስ አበባ ከተማ ያሉ የትምህርት ተቋማት፤ ከአጠቃላይ ወርሃዊ ገቢያቸው 35 በመቶ እንዲከፍሉ የሚያስገድድ ደንብ ተዘጋጀ። ተቋማቱ የከተማይቱ የትምህርት ቢሮ ካስቀመጠው አሰራር ውጪ የማጠናከሪያ ትምህርት ሲሰጡ ከተገኙም፤ ከወርሃዊ ገቢያቸው ተመሳሳይ መጠን ያለው ገንዘብ ለመንግስት ማስገባት ይጠበቅባቸዋል።
“ለአንድ ጊዜ ብቻ”...
በጋሞ ዞን የመሬት ናዳ ከአንድ ቤተሰብ አምስት ሰዎች ህይወታቸውን ማጣታቸውን የአካባቢው አስተዳዳሪ ገለጹ
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል፣ ጋሞ ዞን በደረሰው የመሬት ናዳ አደጋ በርካታ ሰዎች ህይወታቸውን ባጡበት የጋጮ ባባ ወረዳ፤ ከአንድ ቤት እስከ “አምስት ሰዎች” መሞታቸውን የወረዳው አስተዳዳሪ ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናገሩ። በአደጋው ከሞቱት ውስጥ እስካሁን ድረስ የ70 ሰዎች አስከሬን መገኘቱን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ገልጿል።
በጋሞ ዞን ባለፈው ሰኞ የካቲት 30 ምሽት እና...
በጋሞ ዞን በተከሰተ የመሬት ናዳ ሳቢያ የ63 ሰዎች ደብዛ ጠፋ
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጋሞ ዞን የተለያዩ ወረዳዎች በተከሰተ የመሬት ናዳ 35 ሰዎች ሲሞቱ፤ የ63 ሰዎች ደብዛ መጥፋቱን የዞኑ አደጋ ስጋት ስራ አመራር ጽህፈት ቤት አስታወቀ። በመሬት ናዳው ህይወታቸውን ያጡ ሰዎች ቁጥር ከፍ ሊል እንደሚችልም ጽህፈት ቤቱ ስጋቱን ገልጿል።
የመሬት ናዳው የተከሰተው፤ በጋሞ ዞን ደጋማ አካባቢዎች ከትላንት ማክሰኞ መጋቢት 1፤ 2018...
ለ10 ዓመት የሚቆይ የኢትዮጵያን ቪዛ፤ በ10 ሺህ ዶላር ክፍያ ለመስጠት የሚያስችል ደንብ በስራ ላይ...
መደበኛ ፓስፖርት ለሚፈልግ አመልካች፤ 50 ሺህ ብር በመክፈል “በቤት ለቤት ልዩ አገልግሎት” በሁለት ቀናት ውስጥ እንዲያገኝ የሚያስችል ደንብ በስራ ላይ ዋለ። ደንቡ ለ10 ዓመታት የሚያገለግል የኢትዮጵያን “ወርቃማ ቪዛ” (Golden Visa) በ10 ሺህ ዶላር ክፍያ ማግኘት የሚቻልበትን አሰራርም በውስጡ አካትቷል።
ይህንን አዲስ አሰራር ለመጀመሪያ ጊዜ ተግባራዊ ያደረገው፤ ከየካቲት 17፤ 2018 ዓ.ም....
ከስፖርት ውርርድ የሚገኝ ገቢን የመሰብሰብ ስልጣን ለተጨማሪ የፌደራል ተቋም ሰጥቷል የተባለ አዋጅ ጥያቄ ተነሳበት
በፌዴራል የስፖርት ልማት እና አስተዳደር የአዋጅ ረቂቅ ላይ የስፖርት ውርርድን በተመለከተ የሰፈረው ድንጋጌ፤ ከገቢዎች ሚኒስቴር እና ከብሔራዊ ሎተሪ አገልግሎት ስልጣን ጋር “ግጭት የሚፈጥር ነው” የሚል ጥያቄ አስነሳ። ድንጋጌው የሀገሪቱ የስፖርት ልማት ከስፖርት ውርርድ በሚገኝ ገቢ እንዴት መደጎም እንዳለበት የሚያመለክት እንጂ፤ የሌሎች መስሪያ ቤቶችን ስልጣን የማይቃረን እንደሆነ ምላሽ ተሰጥቷል።
ይህ ምላሽ...
የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት ተዋጊዎች “የጦር ወንጀሎች” ሊሆኑ የሚችሉ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶችን መፈጸማቸውን አምነስቲ ኢንተርናሽናል...
በኦሮሚያ ክልል ከ2011 ዓ.ም. ጀምሮ እየተካሄደ ባለው ግጭት ራሱን የኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት (ኦነሰ) ብሎ የሚጠራው ታጣቂ ቡድን፤ “የጦር ወንጀሎች” ሊሆኑ የሚችሉ በርካታ የሰብአዊ መብት ጥሰቶች መፈጸሙን አምነስቲ ኢንተርናሽናል አስታወቀ። ሰራዊቱ በሴቶችና ልጃገረዶች ላይ “በቡድን አስገድዶ መድፈር” የደረሰ ጾታዊ ጥቃት፣ “የወሲብ ባርነት”፣ “ከህግ ውጭ ግድያ”፤ “ስቅየት” እና “የሲቪል ንብረት ውድመት”...
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በድጋፍ መልክ የሚሰበሰቡ ሀብቶችን ለመቆጣጠር የሚያስችል መመሪያ አዘጋጀ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በስሩ የሚገኙ ተቋማት ለድጋፍ የሚሰበስቡትን ገንዘብ፤ ለዚሁ ተግባር በተከፈተ የባንክ ሒሳብ ውስጥ በ24 ሰዓት ውስጥ ገቢ እንዲያደርጉ የሚያስገድድ አዲስ ረቂቅ መመሪያ አዘጋጀ። ከህዝብ፣ ከመንግስት እና ከበጎ አድራጎት ለጋሾች የሚሰበሰበው ይህን መሰሉ ሀብት መመዝገብ ያለበት፤ የከተማ አስተዳደሩ በሚከተለው የሒሳብ አያያዝ ሥርዓት መሠረት እንደሆነም መመሪያው ያዝዛል።
“የድጋፍ ሀብት...











































