ዜና
በአማራ ክልል በተጣለ የእንቅስቃሴ ገደብ ምክንያት በባህር ዳር ያሉ የህዝብ ማመላለሻ አሽከርካሪዎች ስራቸውን አቁመው...
የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ (አፋብን) የተሰኘው ታጣቂ ኃይል በአማራ ክልል ለአምስት ቀናት የሚቆይ የእንቅስቃሴ እገዳ መጣሉን ተከትሎ፤ ከባህር ዳር ወደ ተለያዩ ከተሞች የሚጓዙ አሽከርካሪዎች በዛሬው ዕለት ስራቸውን ማቆማቸውን ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናገሩ። በጎንደር እና በደብረ ማርቆስ ከተሞች የሚገኙ የህዝብ ማመላለሻ አውቶቡስ መናኸሪያዎችም በተመሳሳይ በዛሬው ዕለት ምንም ዓይነት ስምሪት አለማስተናገዳቸውን የዓይን...
በትግራይ ክልል ካለው የግዳጅ አፈሳ ያመለጡ የዓይን እማኞች “እስር”፣ “ድብደባ” እና “ግድያ” ጭምር እየተፈጸመ...
የአዲግራት ከተማ ነዋሪ የሆነው የ27 ዓመቱ ወጣት ጎይቶም ገብረስላሴ*፤ ከመቐለ እና ከመኖሪያ ከተማው የሚገዛቸውን ቡና እና በርበሬ ወደ ዛላንበሳ ከተማ እየወሰደ በመሸጥ የሚተዳደር ነው። ጎይቶም በትግራይ ክልል እና በኤርትራ ድንበር ወደምትገኘው ዛላንበሳ በሳምንት ሁለት ጊዜ እየተመላለሰ የንግድ ስራውን ሲያከናወን፤ ከዚህ ቀደም የከፋ ችግር አልገጠመውም።
በዚሁ ከተማ በሚገኝ ሻይ ቤት ውስጥ...
“ብልጽግና ፓርቲ የመንግስት ስልጣንን ይዣለሁ ብሎ ስልጣን በሌላ መንገድ ለመቀጠል ፈጽሞ አያስብም” – አዳነች...
ገዢው ብልጽግና ፓርቲ “የመንግስት ስልጣንን ይዣለሁ ብሎ ስልጣን በሌላ መንገድ ለመቀጠል ፈጽሞ አያስብም” ሲሉ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ተናገሩ። በሚቀጥለው ሳምንት በሚካሄደው ምርጫ የከተማይቱ ነዋሪ ለፓርቲው ድምጽ እንዲሰጥ ለማሳመን “በብዙ መንገድ እየሰራ” መሆኑንም ገልጸዋል።
ከንቲባዋ ይህን የገለጹት ዛሬ ማክሰኞ ማለዳ በአዲስ አበባው መስቀል አደባባይ በተከናወነው የብልጽግና ፓርቲ የምረጡኝ...
ኢትዮ ቴሌኮም በኢትዮጵያ ሰነደ መዋዕለ ንዋይ ገበያ መመዝገቡን ይፋ አደረገ
መንግስታዊው የቴሌኮም አገልግሎት አቅራቢ ተቋም ኢትዮ ቴሌኮም በኢትዮጵያ ሰነደ መዋዕለ ንዋይ ገበያ (ESX) ላይ የተመዘገበ አራተኛው ኩባንያ ሆነ። ተቋሙ በዚህ ገበያ ላይ መመዝገቡን ይፋ ያደረገው ከኢትዮጵያ ሰነደ መዋዕለ ንዋይ ገበያ ጋር በመተባበር ዛሬ ማክሰኞ ግንቦት 18፤ 2018 ዓ.ም. በአዲስ አበባው ስካይላይት ሆቴል በሰጠው የጋራ መግለጫ ነው።
እስካሁን በሀገሪቱ የመጀመሪያውና ብቸኛው...
ከደቡብ ሱዳን ሰንደቅ ዓላማ ጋር የሚመሳሰል ባንዲራ የያዘ የጋምቤላ ፖሊስ የደንብ ልብስ እንዲስተካከል ታዘዘ ...
ለጋምቤላ ክልል የአድማ ብተና ፖሊስ አባላት በአዲስ መልክ የተዘጋጀ የደንብ ልብስ፤ ከደቡብ ሱዳን ሰንደቅ ዓላማ ጋር የሚመሳሰል ባንዲራ በመያዙ ማስተካከያ እንዲደረግበት ትዕዛዝ ተላለፈ። ትዕዛዙን ከትላንት በስቲያ ቅዳሜ ለአባላቱ ያስተላለፈው የጋምቤላ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ነው።
የአድማ ብተና ፖሊስ አባላት ይጠቀሙበት የነበረው የደንብ ልብስ ላይ ለውጥ እንዲደረግ ውሳኔ ያሳለፈው፤ በክልሉ ከወራት በፊት...
በሱዳን ያለው ጦርነት በጎረቤት ሀገራት ላይ “አለመረጋጋትን ቀስቅሷል” – ፔካ ሐቪስቶ
የ68 ዓመቱ የቀድሞው የፊንላንድ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ፔካ ሐቪስቶ፤ በኢትዮጵያውያን ዘንድ በይበልጥ የሚታወቁት በትግራይ ጦርነት ወቅት ይሰጧቸው በነበሩ ቀጥተኛ እና አነጋጋሪ አስተያየቶች ነበር። በጦርነቱ የመጀመሪያዎቹ ወራት የአውሮፓ ህብረት የኢትዮጵያ ልዩ ልዑክ የነበሩት ሐቪስቶ፤ ከኢትዮጵያ ከፍተኛ ባለስልጣናት ጋር በተደጋጋሚ በመገናኘት ለግጭቱ መፍትሔ ለማበጀት ሲጥሩ ከርመዋል።
በዚሁ ኃላፊነታቸው ወቅት የትግራይ ክልልን የመጎብኘት...
በትግራይ ክልል “በአጭር ጊዜ በህዝብ የተመረጠ መንግስት እንዲኖር” ለማድረግ ያለመ ምክር ቤት ተቋቋመ
በትላንትናው ዕለት በአዲስ አበባ በይፋ የተመሰረተው የትግራይ “የሰላም እና የለውጥ ምክር ቤት” ዋና ዓላማ፤ በክልሉ “በአጭር ጊዜ ውስጥ በህዝብ የተመረጠ መንግስት እንዲኖር ማድረግ” መሆኑን ዴሞክራሲያዊ ስምረት ትግራይ ፓርቲ (ስምረት) ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ገለጸ። ምክር ቤቱ እስከ 40 የሚደርሱ አባላት የሚይዝ ሲሆን አስተባባሪ ኮሚቴም ተዋቅሮለታል።
በትግራይ ክልል የሚንቀሳቀሱ የፖለቲካ ፓርቲዎችን፣ ታዋቂ ግለሰቦችን፣...
የኢትዮጵያን የኢኮኖሚ እድገት “ ‘አላየንም፣ አልሰማንም’ አትበሉ” – ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ
ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ በተለያዩ ጊዜያት በሚያደርጓቸው ንግግሮች፤ ዓለም በኢትዮጵያ “እድገት እና ለውጥ ቢደመምም” በርካታ ኢትዮጵያውያን ግን የተሰራውን ስራ “በቅጡ ለመገንዘብ እና ለማድነቅ እንደሚያዳግታቸው” ሲናገሩ ተደምጠዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ትላንት ቅዳሜ ግንቦት 8፤ 2018 በተካሄደ አንድ ሁነት ላይ ባደረጉት ንግግርም ይህንኑ አቋማቸውን ደግመውታል።
አብይ ንግግሩን ያደረጉት፤ በአዲስ አበባ ከተማ የተገነባው የገላን...
በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በህዝብ ማመላለሻ አውቶብሶች እና ሌሎች ተሽከርካሪዎች ላይ በተፈጸመ ጥቃት ቢያንስ 30...
በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ወደ ግልገል በለስ ከተማ በመጓዝ ላይ በነበሩ የህዝብ ማመላለሻ አውቶብሶች እና ሌሎች ተሽከርካሪዎች ላይ ትላንት ማክሰኞ ጠዋት ታጣቂዎች ባደረሱት ጥቃት ቢያንስ 30 ሰዎች መገደላቸውን እና በርካቶች መቁሰላቸውን የዓይን እማኞች እና የአካባቢው የፓርላማ ተወካይ ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናገሩ። የትላንቱን ጥቃት በተመለከተ መረጃ እንደደረሰው የገለጸው የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ)፤...
ብልጽግና ፓርቲ በአምስት ክልሎች መንግስት መመስረት የሚያስችል የዕጩዎች ብዛት በብቸኝነት ይዞ መቅረቡን የምርጫ ቦርድ...
የኦሮሚያ፣ አማራ፣ ቤኒሻንጉል ጉሙዝ፣ ጋምቤላ፣ ሐረሪ ክልሎች እና የድሬዳዋ ከተማ መስተዳድር ምክር ቤቶች ካሏቸው መቀመጫዎች መካከል ከግማሽ በላይ ዕጩዎችን ያቀረበው ገዢው ብልጽግና ፓርቲ መሆኑን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ይፋ ያደረገው ሰነድ አመለከተ። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ብልጽግና ፓርቲ በተወዳዳሪ ዕጩ ብዛት በተቃዋሚዎች የተበለጠበት ብቸኛው ምክር ቤት ሆኗል።
“ምርጫ 2018 –...
ወደ መቐለ ተጉዞ የነበረው የኢትዮጵያ አየር መንገድ አውሮፕላን፤ ወደ አዲስ አበባ ተመልሶ ያረፈው ለምንድን...
ዛሬ ቅዳሜ ጠዋት ወደ መቐለ በረራ ያደረገ የኢትዮጵያ አየር መንገድ አውሮፕላን፤ በአሉላ አባ ነጋ አየር ማረፊያ በሚገኝ የኮሚኒኬሽን መሳሪያ ብልሽት ምክንያት ወደ አዲስ አበባ ተመልሶ ለማረፍ መገደዱን አንድ የአየር መንገዱ ኃላፊ እና መንገደኞች ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናገሩ። መንገደኞቹ ከሰዓታት ቆይታ በኋላ በዚያው አውሮፕላን መቐለ መድረሳቸውን ገልጸዋል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዛሬ እና...
በነዳጅ የሚሰሩ 1,200 አውቶብሶችን ወደ ጋዝ ተጠቃሚነት ለመቀየር 1.4 ቢሊዮን ብር በጀት ያስፈልጋል ተባለ
በአዲስ አበባ ከተማ የሚገኙ፣ በነዳጅ የሚሰሩ 1,200 የህዝብ ማመለሻ አውቶብሶችን ሞተር፤ በኢትዮጵያ መመረት የጀመረውን የተፈጥሮ ጋዝ እንዲጠቀሙ ለመቀየር 1.4 ቢሊዮን ብር በጀት እንደሚያስፈልግ የከተማይቱ ትራንስፖርት ቢሮ ገለጸ። በመዲናይቱ የሚገኙ አውቶብሶችን ከነዳጅ ወደ ተፈጥሮ ጋዝ ተጠቃሚነት የመቀየር ሙከራ መጀመሩንም ቢሮው አስታውቋል።
የቢሮው ኃላፊ አቶ ያብባል አዲስ ይህን ያስታወቁት፤ ዛሬ አርብ ሚያዝያ 30፤...
ገዢው ብልጽግና ፓርቲ ለ64 የፓርላማ መቀመጫዎች ብቻውን ለምርጫ መቅረቡ ታወቀ
ገዢው ብልጽግና ፓርቲ በመጪው ግንቦት መጨረሻ በሚደረገው ምርጫ፣ በአምስት ክልሎች በሚገኙ 64 የምርጫ ክልሎች ብቻውን ለፓርላማ እንደሚወዳደር የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በትላትንናው ዕለት ይፋ ያደረገው ሰነድ አመለከተ። ከእነዚህ የምርጫ ክልሎች ውስጥ አርባ ስድስቱ በኦሮሚያ፣ አስራ አንዱ ደግሞ በአማራ ክልል የሚገኙ ናቸው።
“ምርጫ 2018 - ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” የተመለከተችው የምርጫ ቦርድ ሰነድ፤...
ከዘንድሮ መጠባበቂያ በጀት 205 ቢሊዮን ብር ገደማ የገንዘብ እጥረት ላጋጠማቸው አስፈጻሚ መስሪያ ቤቶች ተሰጠ...
የፌደራል መንግስት ለዘንድሮው በጀት ዓመት ለመጠባበቂያነት ከያዘው 269 ቢሊዮን ብር ውስጥ 76 በመቶውን ያዋለው፤ የበጀት እጥረት ላጋጠማቸው የአስፈጻሚ መስሪያ ቤቶች ፕሮግራሞች እና ተቋማቱ በበጀት ዝግጅት ጊዜያት ላላካተቷቸው ስራዎች መሆኑን የገንዘብ ሚኒስቴር አስታወቀ። ሚኒስቴሩ ባለፉት ዘጠኝ ወራት ለፌደራል መንግስት መስሪያ ቤቶች የከፈለው የገንዘብ መጠን 847.9 ቢሊዮን ብር እንደሆነም ጨምሮ ገልጿል።
ይህ የተገለጸው...
በ2012 ዓ.ም የተመረጠው የትግራይ ክልል ምክር ቤት፤ ዶ/ር ደብረጽዮን ገብረሚካኤል ክልሉን እንዲመሩ ሾመ
ከስድስት ዓመት በተካሄደው አወዛጋቢ ምርጫ የተመረጠው የትግራይ ክልል ምክር ቤት፤ ዛሬ ማክሰኞ ሚያዝያ 27፤ 2018 ባደረገው ስብስባ ዶ/ር ደብረጽዮን ገብረሚካኤልን የክልሉ ፕሬዝዳንት አድርጎ ሾመ። በህወሓት ማዕከላዊ ኮሚቴ ውሳኔ ወደ ስራ እንዲመለስ የተደረገው ይኸው ምክር ቤት፤ ወ/ሮ ኪሮስ ሐጎስን አፈ ጉባኤ፣ ወ/ሮ ምህረት በርሀን ደግሞ ምክትል አፈጉባኤ አድርጎ መርጧል።
በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ...









































