ሰሞነኛ ጉዳዮች
ህወሓት ከፌደራል መንግስት ሊደራደር የሚችለው “በሶስተኛ ሀገር” እንደሆነ የፓርቲው ጽህፈት ቤት ኃላፊ ጥቆማ ሰጡ
ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) ከፌደራል መንግስት ጋር የሚደራደር ከሆነ በአዲስ አበባ ከተማ ሳይሆን “በሌላ ሶስተኛ ሀገር” እንደሚሆን ለአሜሪካ ማሳወቁን የፓርቲው ጽህፈት ቤት ኃላፊ ፈትለወርቅ ገብረእግዚአብሔር ተናገሩ። የአሜሪካ መንግስት “ቪዛ መከልከል ይቅር እና ሌላ ቢያደርግም”፤ “የትግራይ ህዝብ ህልውናን ለማረጋገጥ” ህወሓት “እስከ መጨረሻ እንደሚታገል” ኃላፊዋ ገልጸዋል።
“ሞንጆሪኖ” በሚለው የቅጽል ስማቸው ይበልጡኑ...
በትግራይ ክልል ካለው የግዳጅ አፈሳ ያመለጡ የዓይን እማኞች “እስር”፣ “ድብደባ” እና “ግድያ” ጭምር እየተፈጸመ...
የአዲግራት ከተማ ነዋሪ የሆነው የ27 ዓመቱ ወጣት ጎይቶም ገብረስላሴ*፤ ከመቐለ እና ከመኖሪያ ከተማው የሚገዛቸውን ቡና እና በርበሬ ወደ ዛላንበሳ ከተማ እየወሰደ በመሸጥ የሚተዳደር ነው። ጎይቶም በትግራይ ክልል እና በኤርትራ ድንበር ወደምትገኘው ዛላንበሳ በሳምንት ሁለት ጊዜ እየተመላለሰ የንግድ ስራውን ሲያከናወን፤ ከዚህ ቀደም የከፋ ችግር አልገጠመውም።
በዚሁ ከተማ በሚገኝ ሻይ ቤት ውስጥ...
በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በህዝብ ማመላለሻ አውቶብሶች እና ሌሎች ተሽከርካሪዎች ላይ በተፈጸመ ጥቃት ቢያንስ 30...
በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ወደ ግልገል በለስ ከተማ በመጓዝ ላይ በነበሩ የህዝብ ማመላለሻ አውቶብሶች እና ሌሎች ተሽከርካሪዎች ላይ ትላንት ማክሰኞ ጠዋት ታጣቂዎች ባደረሱት ጥቃት ቢያንስ 30 ሰዎች መገደላቸውን እና በርካቶች መቁሰላቸውን የዓይን እማኞች እና የአካባቢው የፓርላማ ተወካይ ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናገሩ። የትላንቱን ጥቃት በተመለከተ መረጃ እንደደረሰው የገለጸው የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ)፤...
በጋምቤላ ክልል የጸጥታ መደፍረስ “ተሳትፎ ነበራቸው” የተባሉ 62 የፖሊስ አባላት ጉዳይ በህግ እየታየ መሆኑ...
በጋምቤላ ክልል ተከስቶ በነበረው የጸጥታ መደፍረስ ወቅት “በጥፋት ድርጊቶች ውስጥ ተሳታፊ መሆናቸው ተረጋግጧል” ከተባሉ 272 የፖሊስ አባላት ውስጥ የ62ቱ ጉዳይ በህግ እየታየ መሆኑን አንድ የክልሉ ከፍተኛ ኃላፊ ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናገሩ። ከዚህ ክስተት ጋር በተያያዘ በአጠቃላይ 642 የፖሊስ እና የአድማ ብተና አባላትን ከስራ ማሰናበቱን የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን አስታውቋል።
ኮሚሽኑ በክልሉ ፖሊሶች...
የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት ተዋጊዎች “የጦር ወንጀሎች” ሊሆኑ የሚችሉ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶችን መፈጸማቸውን አምነስቲ ኢንተርናሽናል...
በኦሮሚያ ክልል ከ2011 ዓ.ም. ጀምሮ እየተካሄደ ባለው ግጭት ራሱን የኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት (ኦነሰ) ብሎ የሚጠራው ታጣቂ ቡድን፤ “የጦር ወንጀሎች” ሊሆኑ የሚችሉ በርካታ የሰብአዊ መብት ጥሰቶች መፈጸሙን አምነስቲ ኢንተርናሽናል አስታወቀ። ሰራዊቱ በሴቶችና ልጃገረዶች ላይ “በቡድን አስገድዶ መድፈር” የደረሰ ጾታዊ ጥቃት፣ “የወሲብ ባርነት”፣ “ከህግ ውጭ ግድያ”፤ “ስቅየት” እና “የሲቪል ንብረት ውድመት”...
በጦርነት ስጋት ከትግራይ ክልል ወጣቶች እየሸሹ ነው
የመቐለ ከተማ ነዋሪው እዮብ* እና ቤተሰቦቹ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በማኅበራዊ ሚዲያ የሚመለከቷቸውና የሚሰሟቸው ወሬዎች፤ በልባቸው ውስጥ አንድ “ትልቅ ስጋት” ዳግም እንዲያንሰራራ አድርጓል። “ዳግም ጦርነት ሊጀመር ይችላል” የሚለው ስጋት በቤታቸው ውስጥ ጥላውን አጥልቷል።
ስጋታቸውን ይበልጥ ያገነነው፤ ከጥቂት ሳምንታት በፊት ወላጅ አባታቸው ለሕክምና ክትትል ወደ አዲስ አበባ ካቀኑ በኋላ ለመመለስ በሚሰናዱበት ወቅት...
ፌስታልን የሚተኩ ምርቶች እጥረት እና መወደድ ሸማቾች እና ነጋዴዎችን አስቸግሯል
ገነት ተስፋሁን በአዲስ አበባ ለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ፊጋ አካባቢ በግለሰብ ቤት ተቀጥራ የምትሠራ ወጣት ናት። ለሳምንት ፍጆታ የሚውል አትክልት እንድትገዛ ባለፈው እሁድ ረፋድ ላይ በአካባቢው አደባባይ ዙሪያ ወደሚገኘው “የእሁድ ገበያ” ትላካለች። የእቃ መያዣ ሳትይዝ ከቤት የወጣችው ገነት፤ ከረጢት መሰል ነገር ወደ ወደሚሸጡ ነጋዴዎች ተጠግታ ዋጋውን ስትጠይቅ የተሰጣት ምላሽ...
ቱርክ በአፍሪካ ቀንድ “አዲስ ግጭቶች” “በፍጹም” ማየት እንደማትፈልግ የሀገሪቱ ፕሬዝዳንት ተናገሩ
ቱርክ በአፍሪካ ቀንድ “አዲስ ግጭቶች” “በፍጹም” ማየት እንደማትፈልግ እና በቀጠናው “ስቃይ ውስጥ በሚገኙ” ሰዎች ላይ “አዲስ ህመም” መጨመር እንደማይገባ የሀገሪቱ ፕሬዝዳንት ረቺብ ጣይብ ኤርዶኻን ተናገሩ። ፕሬዝዳንቱ የአፍሪካ ቀንድ የውጭ ኃይሎች “የመፋለሚያ ሜዳ” ሊሆን እንደማይገባም አሳስበዋል።
የቱርኩ ፕሬዝዳንት ማሳሰቢያውን የሰጡት ከጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ጋር በሰጡት የጋራ ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ነው።...
የምርጫ ቦርድ የዲጂታል ምዝገባ ስርዓት በሰባት ፖለቲካ ፓርቲዎች ተቃውሞ ቀረበበት
በመጪው ሀገር አቀፍ ምርጫ ለውድድር የሚቀርቡ ዕጩዎችን ለመመዝገብ የተዘጋጀው የዲጂታል ስርዓት፤ ተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎችን “ከፉክክር ሜዳው በማውጣት ህዝብን አማራጭ አሳጥቶ ለመግዛት የታሰበ የፖለቲካ ሴራ ነው” የሚል ነቀፋ ቀረበበት። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በበኩሉ፤ የምርጫ ሂደቱን “ለመጉዳት” በመስሪያ ቤቱ “ሆን ተብሎ የሚደረግ ተግባር የለም” ሲል አስተባብሏል።
ዛሬ አርብ ጥር 15፤ 2018...
የኢትዮጵያ የአቪዬሽን ደህንነትን የተመለከተው የአዋጅ ማሻሻያ ምን ለውጦችን ይዟል?
ከ20 ዓመት በላይ በሥራ ላይ የቆየውን “የኢትዮጵያ አቪዬሽን ደህንነት አዋጅ” የሚያሻሻል የአዋጅ ረቂቅ፤ ትላንት ሐሙስ ጥር 14፣ 2018 በተካሄደው የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ስብሰባ ላይ ቀርቧል። የአዋጅ ረቂቁ ጉዳዩ ለሚመለከታቸው የፓርላማው ቋሚ ኮሚቴዎች የተመራው፤ ውይይት ሳይካሄድበት እና አስተያየትም ሆነ ጥያቄ ሳይቀርብበት ነው።
የህግ ረቂቁ በነባሩ አዋጅ ውስጥ ያልተካተቱ አዳዲስ...
“ከእያንዳንዱ ግጭት ዕድል ማውጣት ነው የሚጠበቅብን” – ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ
ኢትዮጵያ ከሰሞኑ በተለያዩ የዓለም አካባቢዎች ያሉ “መናጦች” እና “መታወኮችን” ባትፈልግም፤ ከእያንዳንዱ ግጭት “ዕድል ፈልቅቃ ማውጣት” እንደሚጠበቅባት ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ተናገሩ። ዓለም ባልተናጠችበት ወቅት “ጥቅም አግኝተን፣ ስትናጥ እንደምንጎዳ ከእነሱ በላይ መጨነቅ የለብንም” ሲሉም ተደምጠዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህን ያሉት “የፋይናንስ እመርታ በኢትዮጵያ” በተሰኘ ኮንፍረንስ ላይ ከታደሙ ተሳታፊዎች ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች በሰጡት...
የአዲስ አበባ አቅመ ደካሞች ስለ በዓል እና ኑሮ ውድነት ምን ይላሉ?
መብራት አልነበረም። በተንቀሳቃሽ ስልክ መብራት ወደ ቤቷ እየመራችን እንድንገባ ጋበዘችን። ‘ሁሉን አቀፍ’ የሆነች አንድ ክፍል ቤቷ ውስጥ፣ ሰፊውን ቦታ የያዘው አልጋ ነው። የልብስ ሳጥን፣ የምግብ ማብሰያ የተወሰኑ ቁሳቁሶች፣ እድሜ የጠገበ መሆኑ የሚያስታውቅ ተካፋች አጠር ያለ መደርደሪያ እና ከላዩ ባለው የግድግዳ ማዕዘን ቁልቁል የሚወርዱ፣ ጭስ ንጣቱን ሊጋርድ በሚታገለው መጋረጃ የተሸፈኑ የቅዱሳን...
በግጭት ውስጥ የሰነበተው የጋምቤላ ክልል ወቅታዊ የጸጥታ ሁኔታ ምን ይመስላል?
በጋምቤላ ክልል አንጻራዊ መረጋጋት መስፈኑን እና ተፈናቃዮች ወደ ቀዬአቸው “እየተመለሱ መሆናቸውን” የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አለሚቱ ኡሞድ ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ገለጹ። የጋምቤላ ከተማ ነዋሪዎች በበኩላቸው አካባቢያቸው ቀስ በቀስ ወደ መደበኛ እንቅስቃሴ እየተመለሰ ቢሆንም ትምህርት ቤቶች አሁንም ዝግ መሆናቸውን እና አልፎ አልፎ ምሽት ላይ የተኩስ ድምጾች እንደሚሰሙ ተናግረዋል።
የክልሉ ዋና መቀመጫ በሆነችው ጋምቤላ...
ሶማሌላንድን በተመለከተ በፓርላማ ለቀረቡ ጥያቄዎች፤ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ምላሽ ሳይሰጡ ቀሩ
እስራኤል ለሶማሌላንድ ከሰጠችው የነጻ ሉዓላዊ ሀገርነት እውቅና በኋላ ዛሬ የመጀመሪያውን ስብሰባ ያደረገው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት፤ ኢትዮጵያ ከሶማሌላንድ ጋር የደረሰችው የመግባቢያ ስምምነት “የት ደረሰ?” የሚል ጥያቄ አነሳ። በመደበኛ ስብሰባው ላይ የተገኙት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ዶ/ር ጌዲዮን ጢሞቴዎስም ሆነ ምክትሎቻቸው ከሶማሌላንድ ጋር በተያያዘ ለተነሱ ጥያቄዎች ምላሽ ሳይሰጡ ቀርተዋል።
ኢትዮጵያ እና ሶማሌላንድ የዛሬ ሁለት...
እስራኤል ለሶማሌላንድ የሀገርነት እውቅና መስጠቷ ለኢትዮጵያ ምን አንድምታ ይኖረዋል?
እስራኤል ከትላንት በስቲያ አርብ ለራስ ገዝ አስተዳደሯ ሶማሌላንድ የሰጠችው የነጻ ሉዓላዊ ሀገርነት እውቅና በኢትዮጵያ ላይ የሚኖረውን አንድምታ በተመለከተ ሁለት የፖለቲካ ምሁራን ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” አስተያየታቸውን ሰጥተዋል። የመጀመሪያው ኢትዮጵያ ከአረቡ ዓለም ጋር ባላት ግንኙነት ዙሪያ በርካታ ጥናቶችን በማድረግ የሚታወቁት ፕሮፌሰር አደም ካሚል ሲሆኑ ሁለተኛው ደግሞ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካል ሳይንስ መምህር...











































