የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር

ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን፤ በመጪው ዓመት ጥር ወር ዋናውን ኮንፍረንስ ለማካሄድ “የሚቻለውን ጥረት እያደረግኩ ነው” አለ 

በሃሚድ አወል የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በመጪው ዓመት ጥር ወር ላይ ዋናውን የምክክር ጉባኤ ለመጥራት “የሚቻለውን ጥረት” እያደረገ መሆኑን አስታወቀ። ኮሚሽኑ ከነገ ነሐሴ 18፤ 2015 ጀምሮ በአዲስ አበባ ከተማ የጉባኤውን ተሳታፊዎች መለየት እንደሚጀምርም ይፋ አድርጓል። ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽኑ ይህን ይፋ ያደረገው፤ ዛሬ ረቡዕ ነሐሴ 17 በዋና ጽህፈት ቤቱ በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ነው። ባለፈው ዓመት ታህሳስ ወር ላይ በአዋጅ የተቋቋመው ሀገራዊ...

በኢትዮጵያ የተለያዩ አካባቢዎች ያሉ ግጭቶች “ያላንዳች ቅደመ ሁኔታ ቆመው” “በአስቸኳይ” በምክክር እንዲፈቱ ጥሪ ቀረበ

በሃሚድ አወል የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በመላው ሀገሪቱ የሚታዩ ግጭቶች “ያላንዳች ቅደመ ሁኔታ ቆመው” “በአስቸኳይ” በምክክር እንዲፈቱ ጥሪ አቀረበ። ኮሚሽኑ ባለድርሻ አካላትን “በማቀራረብ፣ የልዩነት አጀንዳዎችን...

የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን፤ ከህብረተሰቡ የሚቀርቡ የምክክር አጀንዳዎችን ከዛሬ ጀምሮ መቀበል እንደጀመረ አስታወቀ  

በአማኑኤል ይልቃል የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች የሚላኩለትን የምክክር አጀንዳዎች ከዛሬ ጀምሮ መቀበል እንደጀመረ አስታወቀ። ኮሚሽኑ በሀገራዊ ምክክሩ ላይ የሚሳተፉ ግለሰቦችን የመለየት ስራን፤...

የሀገራዊ ምክክር ሂደት መዘግየት፤ በፓርላማ ቋሚ ኮሚቴ ስብሰባ ጥያቄ አስነሳ

በሃሚድ አወል በኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን አመቻችነት የሚካሄደው የሀገራዊ ምክክር ሂደት መዘግየት፤ በተወካዮች ምክር ቤት የዲሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ስብሰባ ጥያቄ አስነሳ። የኮሚሽኑ ዋና ኮሚሽነር ፕ/ር መስፍን አርዓያ፤ ህዝብ እና መንግስት ከኮሚሽኑ የሚጠብቀው “በጣም ከፍተኛ” መሆን “ትልቅ ተግዳሮት” እንደሆነ ለቋሚ ኮሚቴው ተናግረዋል።  ፕ/ር መስፍን ይህን ምላሽ የሰጡት በዋና ኮሚሽነርነት የሚመሩትን፤ የሀገራዊ...

አራት የፖለቲካ ፓርቲዎች፤ ለሀገራዊ ምክክር “አማራጮችን ለማቅረብ” የተቋቋመውን “ኮከስ” ተቀላቀሉ 

በሃሚድ አወል አራት የፖለቲካ ፓርቲዎች እና አንድ የፓርቲዎች ትብብር፤ ባለፈው ዓመት ግንቦት ወር የተቋቋመውን የተቃዋሚ ፖለቲካ ፓርቲዎች ስብስብ ተቀላቀሉ። “የተቃዋሚ ፓርቲዎች ኮከስ” የተሰኘውን ይህን ስብስብ የተቀላቀሉ ፓርቲዎች እና ነባሮቹ የኮከሱ አባላት ከትላንት በስቲያ ቅዳሜ የካቲት 25፤ 2015 በአዲስ አበባ ከተማ የመግባቢያ ሰነድ ተፈራርመዋል። አስር የፖለቲካ ፓርቲዎች እና የኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዴሞክራሲያዊ አንድነት...

የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ኮሚሽነሮች፤ ከዳያስፖራ ኢትዮጵያውያን ጋር ለመወያየት ወደ ውጭ ሀገራት ሊጓዙ ነው 

በሃሚድ አወል የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በውጭ ሀገር ከሚገኙ ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ጋር ለመወያያት የውጭ ሀገር ጉዞዎችን እንደሚያደርግ አስታወቀ። ኮሚሽኑ “በጥቂት ቀናት” ውስጥ ከዳያስፖራዎች ጋር በበይነ መረብ አማካኝነት ስብሰባዎችን እንደሚያደርግም ገልጿል። ከአንድ ዓመት በፊት በአዋጅ የተቋቋመው የሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን፤ የምክክር ተሳታፊዎችን ለመለየት ትኩረት ከሚያደርግባቸው የህብረተሰብ ክፍሎች መካከል አንደኛው ዳያስፖራ ኢትዮጵያውያን...

የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን፤ የምክክር ተሳታፊዎችን የመለየት ስራ ከሶስት ሳምንት በኋላ ሊጀምር ነው 

በሃሚድ አወል የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከሶስት ሳምንት በኋላ የምክክር ተሳታፊዎች የመለየት ስራን በወረዳ ደረጃ እንደሚጀምር አስታወቀ። ኮሚሽኑ በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች ከባለድርሻ አካላት ጋር ሲያደርጋቸው የነበሩ የግብዓት ማሰባሰቢያ ውይይቶችን ማጠናቀቁንም ገልጿል። ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽኑ ይህን የገለጸው ዛሬ ሰኞ ጥር 15 በአዲስ አበባው ኃይሌ ግራንድ ሆቴል እያካሄደ ባለው “የመጨረሻው የባለድርሻ አካላት ውይይት”...

የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን፤ ፓርላማውም ጭምር አጀንዳ ሊቀርጽለት እንደማይችል አሳሰበ 

በሃሚድ አወል ከአንድ ዓመት ገደማ በፊት በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በአዋጅ የተቋቋመው የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን፤ ፓርላማውም ቢሆን አጀንዳዎች እንዲቀርጽለት እንደማይፈልግ አስታወቀ። አጀንዳ የማሰባሰብ እና የመቅረጽ ኃላፊነት በአዋጅ የተሰጠው ለኮሚሽኑ ብቻ መሆኑንም ገልጿል። በአስራ አንድ ኮሚሽነሮች የሚመራው ኮሚሽን ይህን ያስታወቀው፤ የስራ አፈጻጸም ሪፖርቱን ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ዛሬ ረቡዕ ህዳር...

የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን የተሳታፊ ልየታ እና አጀንዳ መረጣን በተመለከተ የግብዓት ማሰባሰቢያ ውይይቶች ማካሄድ...

በሃሚድ አወል የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በመጪው ህዳር ወር ለማካሄድ ላቀደው ሀገር አቀፍ ምክክር ተሳታፊዎች የሚለዩበት እና አጀንዳዎች የሚመረጡበትን አካሄድ በተመለከተ ከተለያዩ ክልሎች ከተውጣጡ ባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት ማካሄድ ጀመረ። በትላንትናው ዕለት በተጀመረው እና ዛሬ በተጠናቀቀው የመጀመሪያው ዙር የግብዓት ማሰባሰቢያ ውይይት የታደሙት ከአፋር፣ ቤኒሻንጉል ጉሙዝ እና ጋምቤላ ክልሎች የተውጣጡ የተለያዩ...

የተመድ የልማት ፕሮግራም ለኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር የሚውል 32.8 ሚሊዮን ዶላር ሊያሰባስብ ነው 

የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የልማት ፕሮግራም (UNDP) በኢትዮጵያ የሚካሄደውን ሀገራዊ ምክክር ለመደገፍ 32.8 ሚሊዮን ዶላር ለማሰባሰብ ማቀዱ ተገለጸ። በቀጣዮቹ ሶስት ዓመታት ከልማት አጋሮች ይሰበሰባል የተባለው ይኸው የድጋፍ ገንዘብ፤ UNDP በሚከፍተው “የፋይናንስ ቋት” አማካኝነት ለኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን ይተላለፋል ተብሏል።  የመንግስታቱ ድርጅት የልማት ፕሮግራም የገንዘብ ድጋፉን ለማድረግ የሚያስችለውን ስምምነት ዛሬ ረቡዕ መስከረም...

የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን የሙከራ ምክክር ለማከናወን ቡድኖችን ወደተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች ሊልክ ነው

በሃሚድ አወል የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን የሙከራ ምክክር ለማድረግ የሚያስችሉ ቡድኖችን በሚቀጥለው ሳምንት ወደተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች ሊያሰማራ ነው። ኮሚሽኑ መጀመሪያውን ዙር ሀገር አቀፍ ውይይት ከሁለት ወራት በኋላ በህዳር ወር አጋማሽ ላይ የማካሄድ ዕቅድ ይዟል።  ከሀገራዊ ምክክር ኮሚሽኑ ከኮሚሽኑ ኮሚሽነሮች አንዱ የሆኑት ዶ/ር ዮናስ አዳዬ፤ ኮሚሽኑ ሀገር አቀፍ ውይይቱን ከመጀመሩ አስቀድሞ “በአነስተኛ...

የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ለ2015 በጀት ዓመት 3.2 ቢሊዮን ብር እንደሚያስፈልገው ገለጸ

በሃሚድ አወል የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በ2015 በጀት ዓመት የያዛቸውን ዕቅዶች ለማስፈጸም 3.2 ቢሊዮን ብር እንደሚያስፈልገው አስታወቀ። ኮሚሽኑ ከዚህ በተጨማሪም በበጀት ዓመቱ ለሚያከናውናቸው ተግባራት የሚውል 208.6 ሚሊዮን ብር ከተለያዩ የልማት አጋሮች ለማሰባሰብ ማቀዱንም ገልጿል።  ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽኑ ይህን ያስታወቀው ትላንት ማክሰኞ ሐምሌ 12፤ 2014 ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አስተባባሪ እና አማካሪ ኮሚቴ...

የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት፤ ነፍጥ ያነገቡ ኃይሎች በሀገራዊ ምክክሩ ላይ እንዲሳተፉ ጠየቀ

በሃሚድ አወል የኢትዮጵያ ፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ነፍጥ ያነገቡ ኃይሎች በሀገራዊ ምክክሩ እንዲሳተፉ ለፓርላማ ጥያቄ አቀረበ። ምክር ቤቱ ጥያቄውን ያቀረበው ከትላንት በስቲያ ማክሰኞ ሚያዚያ 18፤ 2014 በተወካዮች ምክር ቤት በተደረገ ውይይት ላይ ነው። የማክሰኞው ውይይት የተካሄደው የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አቶ ታገሰ ጫፎ ለፖለቲካ ፓርቲዎች እና ለጋራ ምክር...

የሀገራዊ የምክከር ኮሚሽን፤ ፍኖተ ካርታ እና ዝርዝር ዕቅድ እንዲያዘጋጅ በፓርላማ ተጠየቀ

በሃሚድ አወል የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን ፍኖተ ካርታ እና ዝርዝር ዕቅድ እንዲያዘጋጅ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ተጠየቀ። ኮሚሽኑ ጥያቄው የቀረበለት ዛሬ ማክሰኞ ሚያዚያ 18፤ 2014 ለምክር ቤቱ አፈ ጉባኤዎች እና የቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢዎች ሪፖርት ካቀረበ በኋላ ነው።  በኮሚሽኑ ሰብሳቢ ፕሮፌሰር መስፍን አርአያ የቀረበው ሪፖርት፤ ኮሚሽኑ እስካሁን ያከናወናቸውን ተግባራት ዘርዝሯል። ኮሚሽኑ ስራዎቹን...

የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት፤ ሁለት ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት ስለ አገራዊ ምክክሩ ሂደት ማብራሪያ...

በሃሚድ አወል የኢትዮጵያ ፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ሁለት ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት ስለ አገራዊ ምክክሩ ሂደት ማብራሪያ እንዲሰጡ ውሳኔ አሳለፈ። በጋራ ምክር ቤቱ አባላት ፊት በአካል ቀርበው ማብራሪያ እንዲሰጡ የተባሉት ባለስልጣናት፤ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አቶ ታገሰ ጫፎ እና የፍትህ ሚኒስትሩ ዶ/ር ጌዲዮን ጢሞቲዮስ ናቸው።  የጋራ ምክር ቤቱ ዛሬ...

ከሶስት ዓመት በፊት የተቋቋሙ የሁለት ኮሚሽኖች ንብረት እና በጀት፤ ለአዲሱ አገራዊ ምክክር ኮሚሽን ሊተላለፍ...

በሃሚድ አወል ከሶስት ዓመት በፊት የተቋቋሙት የእርቀ ሰላም እንዲሁም የአስተዳደር ወሰን እና የማንነት ጉዳዮች ኮሚሽኖች ንብረት፣ ቢሮ እና በጀት፤ አዲስ ለተቋቋመው የኢትዮጵያ አገራዊ ምክክር ኮሚሽን እንዲተላለፍ ተወሰነ። አገራዊ የምክክር ኮሚሽኑ፤ በአዲስ አበባ አሜሪካ ኤምባሲ አጠገብ በሚገኘው የሁለቱ ኮሚሽኖች ቅጥር ግቢ ውስጥ ቢሮ ማደራጀት መጀመሩን የተቋማቱ ኃላፊዎች ተናግረዋል።  ከሁለት ወር በፊት በአዋጅ...

“ከማንም ጋር፤ በውይይት በንግግር የሚፈታ ችግር ካለ መንግስት በሩ ክፍት ነው” – ጠቅላይ ሚኒስትር...

በሃሚድ አወል ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ችግርን በውይይት እና በንግግር ለመፍታት መንግስት በሩ ክፍት መሆኑን ለፓርላማ አባላት ተናገሩ። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ዛሬ ማክሰኞ የካቲት 15 ለተወካዮች ምክር ቤት አባላት በሰጡት ማብራሪያ ከህወሓት ጋር እስካሁን የተጀመረ ድርድር አለመኖሩን ገልጸዋል።   ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህን የተናገሩት የተቃዋሚው የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) የፓርላማ ተወካዩ አቶ ክርስቲያን...

የተወካዮች ምክር ቤት የኢትዮጵያ አገራዊ ምክክር ኮሚሽን ኮሚሽነሮችን ሹመት አጸደቀ

በሃሚድ አወል የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ሰኞ የካቲት 14 ባካሄደው አስቸኳይ ስብሰባ፤ የኢትዮጵያ አገራዊ ምክክር ኮሚሽንን 11 ኮሚሽነሮች ሹመት አጸደቀ። ምክር ቤቱ የኮሚሽነሮችን ሹመት ያጸደቀው በአብላጫ ድምጽ ነው።  “ሁሉን አቀፍ እና አካታች ምክክር ያካሄዳል” ለተባለው ኮሚሽን የሚያገለግሉት ኮሚሽነሮች ሹመት ከፓርላማ አባላት ምንም ተቃውሞ አልገጠመውም። በዛሬው አስቸኳይ ስብሰባ ላይ ከተገኙት 335...