የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር

አራት የፖለቲካ ፓርቲዎች፤ ለሀገራዊ ምክክር “አማራጮችን ለማቅረብ” የተቋቋመውን “ኮከስ” ተቀላቀሉ 

በሃሚድ አወል አራት የፖለቲካ ፓርቲዎች እና አንድ የፓርቲዎች ትብብር፤ ባለፈው ዓመት ግንቦት ወር የተቋቋመውን የተቃዋሚ ፖለቲካ ፓርቲዎች ስብስብ ተቀላቀሉ። “የተቃዋሚ ፓርቲዎች ኮከስ” የተሰኘውን ይህን ስብስብ የተቀላቀሉ ፓርቲዎች እና ነባሮቹ የኮከሱ አባላት ከትላንት በስቲያ ቅዳሜ የካቲት 25፤ 2015 በአዲስ አበባ ከተማ የመግባቢያ ሰነድ ተፈራርመዋል። አስር የፖለቲካ ፓርቲዎች እና የኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዴሞክራሲያዊ አንድነት መድረክ (መድረክ) የተሰኘው የፓርቲዎች ትብብር፤ በኢትዮጵያ ለሚካሄደው ሀገራዊ ምክክር “አማራጮችን”...

የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ኮሚሽነሮች፤ ከዳያስፖራ ኢትዮጵያውያን ጋር ለመወያየት ወደ ውጭ ሀገራት ሊጓዙ ነው 

በሃሚድ አወል የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በውጭ ሀገር ከሚገኙ ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ጋር ለመወያያት የውጭ ሀገር ጉዞዎችን እንደሚያደርግ አስታወቀ። ኮሚሽኑ “በጥቂት ቀናት” ውስጥ ከዳያስፖራዎች...

የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን፤ የምክክር ተሳታፊዎችን የመለየት ስራ ከሶስት ሳምንት በኋላ ሊጀምር ነው 

በሃሚድ አወል የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከሶስት ሳምንት በኋላ የምክክር ተሳታፊዎች የመለየት ስራን በወረዳ ደረጃ እንደሚጀምር አስታወቀ። ኮሚሽኑ በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች ከባለድርሻ አካላት ጋር ሲያደርጋቸው...

የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን፤ ፓርላማውም ጭምር አጀንዳ ሊቀርጽለት እንደማይችል አሳሰበ 

በሃሚድ አወል ከአንድ ዓመት ገደማ በፊት በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በአዋጅ የተቋቋመው የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን፤ ፓርላማውም ቢሆን አጀንዳዎች እንዲቀርጽለት እንደማይፈልግ አስታወቀ። አጀንዳ የማሰባሰብ እና የመቅረጽ ኃላፊነት በአዋጅ የተሰጠው ለኮሚሽኑ ብቻ መሆኑንም ገልጿል። በአስራ አንድ ኮሚሽነሮች የሚመራው ኮሚሽን ይህን ያስታወቀው፤ የስራ አፈጻጸም ሪፖርቱን ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ዛሬ ረቡዕ ህዳር...

የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን የተሳታፊ ልየታ እና አጀንዳ መረጣን በተመለከተ የግብዓት ማሰባሰቢያ ውይይቶች ማካሄድ...

በሃሚድ አወል የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በመጪው ህዳር ወር ለማካሄድ ላቀደው ሀገር አቀፍ ምክክር ተሳታፊዎች የሚለዩበት እና አጀንዳዎች የሚመረጡበትን አካሄድ በተመለከተ ከተለያዩ ክልሎች ከተውጣጡ ባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት ማካሄድ ጀመረ። በትላንትናው ዕለት በተጀመረው እና ዛሬ በተጠናቀቀው የመጀመሪያው ዙር የግብዓት ማሰባሰቢያ ውይይት የታደሙት ከአፋር፣ ቤኒሻንጉል ጉሙዝ እና ጋምቤላ ክልሎች የተውጣጡ የተለያዩ...

የተመድ የልማት ፕሮግራም ለኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር የሚውል 32.8 ሚሊዮን ዶላር ሊያሰባስብ ነው 

የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የልማት ፕሮግራም (UNDP) በኢትዮጵያ የሚካሄደውን ሀገራዊ ምክክር ለመደገፍ 32.8 ሚሊዮን ዶላር ለማሰባሰብ ማቀዱ ተገለጸ። በቀጣዮቹ ሶስት ዓመታት ከልማት አጋሮች ይሰበሰባል የተባለው ይኸው የድጋፍ ገንዘብ፤ UNDP በሚከፍተው “የፋይናንስ ቋት” አማካኝነት ለኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን ይተላለፋል ተብሏል።  የመንግስታቱ ድርጅት የልማት ፕሮግራም የገንዘብ ድጋፉን ለማድረግ የሚያስችለውን ስምምነት ዛሬ ረቡዕ መስከረም...

የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን የሙከራ ምክክር ለማከናወን ቡድኖችን ወደተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች ሊልክ ነው

በሃሚድ አወል የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን የሙከራ ምክክር ለማድረግ የሚያስችሉ ቡድኖችን በሚቀጥለው ሳምንት ወደተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች ሊያሰማራ ነው። ኮሚሽኑ መጀመሪያውን ዙር ሀገር አቀፍ ውይይት ከሁለት ወራት በኋላ በህዳር ወር አጋማሽ ላይ የማካሄድ ዕቅድ ይዟል።  ከሀገራዊ ምክክር ኮሚሽኑ ከኮሚሽኑ ኮሚሽነሮች አንዱ የሆኑት ዶ/ር ዮናስ አዳዬ፤ ኮሚሽኑ ሀገር አቀፍ ውይይቱን ከመጀመሩ አስቀድሞ “በአነስተኛ...

የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ለ2015 በጀት ዓመት 3.2 ቢሊዮን ብር እንደሚያስፈልገው ገለጸ

በሃሚድ አወል የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በ2015 በጀት ዓመት የያዛቸውን ዕቅዶች ለማስፈጸም 3.2 ቢሊዮን ብር እንደሚያስፈልገው አስታወቀ። ኮሚሽኑ ከዚህ በተጨማሪም በበጀት ዓመቱ ለሚያከናውናቸው ተግባራት የሚውል 208.6 ሚሊዮን ብር ከተለያዩ የልማት አጋሮች ለማሰባሰብ ማቀዱንም ገልጿል።  ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽኑ ይህን ያስታወቀው ትላንት ማክሰኞ ሐምሌ 12፤ 2014 ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አስተባባሪ እና አማካሪ ኮሚቴ...

የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት፤ ነፍጥ ያነገቡ ኃይሎች በሀገራዊ ምክክሩ ላይ እንዲሳተፉ ጠየቀ

በሃሚድ አወል የኢትዮጵያ ፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ነፍጥ ያነገቡ ኃይሎች በሀገራዊ ምክክሩ እንዲሳተፉ ለፓርላማ ጥያቄ አቀረበ። ምክር ቤቱ ጥያቄውን ያቀረበው ከትላንት በስቲያ ማክሰኞ ሚያዚያ 18፤ 2014 በተወካዮች ምክር ቤት በተደረገ ውይይት ላይ ነው። የማክሰኞው ውይይት የተካሄደው የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አቶ ታገሰ ጫፎ ለፖለቲካ ፓርቲዎች እና ለጋራ ምክር...

የሀገራዊ የምክከር ኮሚሽን፤ ፍኖተ ካርታ እና ዝርዝር ዕቅድ እንዲያዘጋጅ በፓርላማ ተጠየቀ

በሃሚድ አወል የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን ፍኖተ ካርታ እና ዝርዝር ዕቅድ እንዲያዘጋጅ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ተጠየቀ። ኮሚሽኑ ጥያቄው የቀረበለት ዛሬ ማክሰኞ ሚያዚያ 18፤ 2014 ለምክር ቤቱ አፈ ጉባኤዎች እና የቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢዎች ሪፖርት ካቀረበ በኋላ ነው።  በኮሚሽኑ ሰብሳቢ ፕሮፌሰር መስፍን አርአያ የቀረበው ሪፖርት፤ ኮሚሽኑ እስካሁን ያከናወናቸውን ተግባራት ዘርዝሯል። ኮሚሽኑ ስራዎቹን...

የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት፤ ሁለት ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት ስለ አገራዊ ምክክሩ ሂደት ማብራሪያ...

በሃሚድ አወል የኢትዮጵያ ፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ሁለት ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት ስለ አገራዊ ምክክሩ ሂደት ማብራሪያ እንዲሰጡ ውሳኔ አሳለፈ። በጋራ ምክር ቤቱ አባላት ፊት በአካል ቀርበው ማብራሪያ እንዲሰጡ የተባሉት ባለስልጣናት፤ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አቶ ታገሰ ጫፎ እና የፍትህ ሚኒስትሩ ዶ/ር ጌዲዮን ጢሞቲዮስ ናቸው።  የጋራ ምክር ቤቱ ዛሬ...

ከሶስት ዓመት በፊት የተቋቋሙ የሁለት ኮሚሽኖች ንብረት እና በጀት፤ ለአዲሱ አገራዊ ምክክር ኮሚሽን ሊተላለፍ...

በሃሚድ አወል ከሶስት ዓመት በፊት የተቋቋሙት የእርቀ ሰላም እንዲሁም የአስተዳደር ወሰን እና የማንነት ጉዳዮች ኮሚሽኖች ንብረት፣ ቢሮ እና በጀት፤ አዲስ ለተቋቋመው የኢትዮጵያ አገራዊ ምክክር ኮሚሽን እንዲተላለፍ ተወሰነ። አገራዊ የምክክር ኮሚሽኑ፤ በአዲስ አበባ አሜሪካ ኤምባሲ አጠገብ በሚገኘው የሁለቱ ኮሚሽኖች ቅጥር ግቢ ውስጥ ቢሮ ማደራጀት መጀመሩን የተቋማቱ ኃላፊዎች ተናግረዋል።  ከሁለት ወር በፊት በአዋጅ...

“ከማንም ጋር፤ በውይይት በንግግር የሚፈታ ችግር ካለ መንግስት በሩ ክፍት ነው” – ጠቅላይ ሚኒስትር...

በሃሚድ አወል ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ችግርን በውይይት እና በንግግር ለመፍታት መንግስት በሩ ክፍት መሆኑን ለፓርላማ አባላት ተናገሩ። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ዛሬ ማክሰኞ የካቲት 15 ለተወካዮች ምክር ቤት አባላት በሰጡት ማብራሪያ ከህወሓት ጋር እስካሁን የተጀመረ ድርድር አለመኖሩን ገልጸዋል።   ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህን የተናገሩት የተቃዋሚው የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) የፓርላማ ተወካዩ አቶ ክርስቲያን...

የተወካዮች ምክር ቤት የኢትዮጵያ አገራዊ ምክክር ኮሚሽን ኮሚሽነሮችን ሹመት አጸደቀ

በሃሚድ አወል የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ሰኞ የካቲት 14 ባካሄደው አስቸኳይ ስብሰባ፤ የኢትዮጵያ አገራዊ ምክክር ኮሚሽንን 11 ኮሚሽነሮች ሹመት አጸደቀ። ምክር ቤቱ የኮሚሽነሮችን ሹመት ያጸደቀው በአብላጫ ድምጽ ነው።  “ሁሉን አቀፍ እና አካታች ምክክር ያካሄዳል” ለተባለው ኮሚሽን የሚያገለግሉት ኮሚሽነሮች ሹመት ከፓርላማ አባላት ምንም ተቃውሞ አልገጠመውም። በዛሬው አስቸኳይ ስብሰባ ላይ ከተገኙት 335...

የአገራዊ ምክክር ኮሚሽን ኮሚሽነሮች ሹመት፤ በነገው የፓርላማ አስቸኳይ ስብሰባ ሊጸድቅ ነው

በሃሚድ አወል የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት፤ የኢትዮጵያ አገራዊ ምክክር ኮሚሽንን በኮሚሽነርነት የሚመሩ የ11 ኮሚሽነሮችን ሹመት ሊያጸድቅ ነው። ምክር ቤቱ ነገ ሰኞ የካቲት 14 በሚያካሄደው አስቸኳይ ስብሰባ፤ የኮሚሽነሮችን ሹመት ማጽደቅ በዋና አጀንዳነት መያዙን ሶስት የፓርላማ አባላት ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” አረጋግጠዋል።  በነገው የምክር ቤቱ አስቸኳይ ስብሰባ፤ የዕጩ ኮሚሽነሮችን ሹመት ለማጽደቅ የቀረበ አራት ገጽ የውሳኔ...

የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት፤ የአገራዊ ምክክሩ ሂደት ለጊዜው ቆሞ በድጋሚ ውይይት እንዲደረግበት ጥያቄ...

በሃሚድ አወል የኢትዮጵያ ፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት የአገራዊ ምክክር ሂደት ለጊዜው “ገታ ተደርጎ” በአጠቃላይ አካሄዱ ላይ በድጋሚ ውይይት እንዲደረግ ጥያቄ አቀረበ። ምክር ቤቱ ይህንን ጥያቄውን ያቀረበው፤ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጽህፈት ቤት እና ለአፈ ጉባኤ ጽህፈት ቤት ባለፈው ሳምንት መጨረሻ ባስገባው ደብዳቤ ነው።  የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤቱ ለሁለቱ ጽህፈት...

የ42 ዕጩ ኮሚሽነሮች ማንነት ታወቀ

የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት፤ ለኢትዮጵያ አገራዊ የምክክር ኮሚሽን በዕጩነት ከተጠቆሙ ግለሰቦች መካከል፤ በኮሚሽኑ ማቋቋሚያ አዋጅ ላይ “በተቀመጠው መስፈርት የተለዩ ናቸው” ያላቸውን 42 ዕጩ ኮሚሽነሮችን ማንነት ዛሬ አርብ ጥር 27 ይፋ አደረገ። ዕጩዎቹ የተለዩት ለኮሚሽነርነት ከተጠቆሙ 632 ግለሰቦች መካከል ነው።   ከዕጩ ኮሚሽነሮቹ መካከል አስራ ሶስቱ ፕሮፌሰሮች ሲሆኑ አስራ ሁለቱ ደግሞ...

የፖለቲካ ፓርቲዎች በፖለቲካዊ እና ሀገራዊ አጀንዳዎች ላይ የሚያደርጉት ውይይት የሚመራበት መመሪያ ጸደቀ

በሃሚድ አወል የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ፤ ህጋዊ ዕውቅና ያገኙ የፖለቲካ ፓርቲዎች በፖለቲካዊ እና ሀገራዊ አጀንዳዎች ላይ የሚያደርጉት ውይይት የሚመራበትን መመሪያ አሻሽሎ አጸደቀ። መመሪያው ከተከታታይ ውይይቶች በኋላ የጸደቀው ዛሬ ጥር 25፤ 2014 ቦርዱ ከፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር ባደረገው ስብሰባ ላይ ነው። የፖለቲካ ፓርቲዎች ውይይትን ለመምራት የመጀመሪያው መመሪያ የወጣው ከሶስት ዓመታት በፊት በ2011 ነበር።...